በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን አዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ከዚህ በታች የተገለፁትን የማሸጊያ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የብሔራዊ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ ማስታወቂያ ቁጥር APPF/NCB/01/19
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን አዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ከዚህ በታች የተገለፁትን የማሸጊያ እቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
1.1. የተለያዩ Carton Label
1.2. የተለያዩ Adhesive Label
1.3. Carton Box 16 Lit/7kgCapacity
1.4. የተለያዩ Plastic Sheet
2. ተጫራቾች የስራ ዘርፍ የሚያሳይ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ለሚከፈልባቸው ዕቃዎች የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ በመንግሥት የግብር ሕግ መሠረት ግብርየመከፈል ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የሚያሳይ ሰርቲፊኬት እና በመንግሥት ግዥ ለመሳተፍ በመንግስት የኤሌክትሮኒክ ሥርዓት ፖርታል ላይ በአቅራቢነት መመዝገቡን የሚያሳይ መረጃ እንደ ቅድመ ሁኔታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
3. ተጫራቾች አዳሚ ቱሉ ባለው የፋብሪከው ዋና መስሪያ ቤት ወይም አዲስ አበባ ቦሌ ሩዋንዳ ከኩዌት ኢምብሲ 10 ሜትር ገባ ብሎ ጅቡቲ ኢምበሲ ፊትለፊት ከሚገኘው ማስተባበሪያ ቢሮ የማይመለስ ብር አምስት መቶ ብቻ (500.00) በመከፈል የጨረታው ማስታወቂያ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
4. ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ ላይ የተጫራቹ ድርጅት ስምና አድራሻ በትክከል ተፅፎ የድርጅቱ ማህተም ያረፈበት መሆን ይኖርበታል፡፡
5. ተጫራቾች ቴከኒካል እና ፋይናንሺያል ሰነዶቻቸውን ኮፒ እና ኦሪጅናሉን በተለያየ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
6. ተጫራቾች ለሚጫረቱበት እቃ በራሳቸው የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በመሙላት በተጫራቹ ድርጅት ኃላፊ ተፈርሞና ማህተም በማድረግ ማቅረብ አለባቸው፡፡
7. ተጫራቾች ለጨረታ ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 2% የጨረታ ማስከበሪያ በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን አዳሚ ቱሉ የፀረ-ተባይ ማዘጋጃ ፋብሪካ ስም የባንከ የከፍያ ትዕዛዝ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ከጨረታው የቴከኒካል ሰነድ ጋር ለብቻው በፖስታ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው፡፡
8. ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሰነዱን እስከ ነሀሴ 3ዐ ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ድረስ የፋብሪከው ዋና መስሪያ ቤት ወይም አዲስ አበባ በሚገኘው ማስተባበሪያ ቢሮ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ መክፈቻው ዕለት ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ አበባ ቦሌ ርዋንዳ በሚገኘው ማስተባበሪያ ቢሮ ይሆናል፡፡
9. ፋብሪካው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- አ.አ ማስተባበሪያ ስልከ ቁጥር 011 662 4656 አ/አ፣ አዳሚ ቱሉ 0464419164 (አ/አ) 0464419287 (ማዞሪያ) 0464419287 (ንግድ ማዞሪያ) ፖሠዓቁ 1206: (አ/አ) 247 (እ/ቱሉ)
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን አዳሚቱሱ የፀረ-ተባይማዘጋጃ ፋብሪካ
