በጨረታ ሁለት (ሎት 2) ፦ የዕቃ ማሰሪያ ቃጫ (String for Packing) ብዛት 1,500 ኪግ ግዥ፣
የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር 021/18
ድርጅታችን ከዚህ በታች በሱት የተዘረዘሩትን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- በጨረታ አንድ (ሎት 1) - Plate Cleaner (የፕሌት ማጽጃ) ብዛት 300 ሊትር ግዥ
- በጨረታ ሁለት (ሎት 2) ፦ የዕቃ ማሰሪያ ቃጫ (String for Packing) ብዛት 1,500 ኪግ ግዥ፣
- በጨረታ ሶስት (ሎት 3):- ክር (Cotton Thread 5,000mts) ብዛት 200 ግዥ
- በጨረታ አራት (ሎት 4) - የጽህፈት መሳሪያዎች ግዥ ማለትም:- Computer Paper (የኮምፒውተር ወረቀት) ብዛት 2,000 ፓኬት፣ Blue Ball Point Pen (ሰማያዊ እስክሪብቶ) ብዛት 7,000፣ Red Ball Point Pen (ቀይ አስክሪብቶ) ብዛት 1,000፣ Pencil (እርሳስ) ብዛት 500፣ Marking Pen (ማርከር) ብዛት 5,000፣ Box file (ፋይል አቃፊ) ብዛት 1,900፣ Scotch Tape Cheque packing big (TAM ትልቁ) ብዛት 1,000 ጥቅል፣ Correcting Fluid (ፍሉድ) ብዛት 300 ቦትስ፣ Paper Clips 33mm (አግራፍ) ብዛት 300 ፓኬት፤ Rubber Band (የብር ማሰሪያ ላስቲክ) ብዛት 500 ኪ.ግ
- የጽዳት መሳሪያዎች ግዥ ማለትም ፤ ባለ 200 ግራም ሳሙና ብዛት 6,000, ቁርጥራጭ ጨርቅ (Hag) ብዛት 2,000 ኪ.ግ፤ ባለ 500 ግራም ቪም ብዛት 300 ቲን፣ ዲቶል (Detol 500ml) ብዛት 400 ቦትል፣ Powder Soap (ባለ 200 ግራም የዱቄት ሳሙና) ብዛት 3,000 ፓኬት እና መወልወያ (Floor Clearing Rag) ብዛት 200
በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ወቅታዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የዕቃ አቅራቢዎች ምዝገባ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፤ የግብር ከፋይ ምስክር ወረቀት እና በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል የታክስ ክሊራንስ ያላቸው ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በድርጅቱ ዋና መ/ቤት (አራት ኪሎ) አዲስ ህንፃ 1ኛ ፎቅ በሚገኘው የዕለት ገንዘብ ተቀባይ የማይመለስ ብር 300.00 ከፍለው በመግዛት ፋይናንሺያል የቴክኒካል የመጫረቻ ሰነዶቻቸውን ዋናውን እና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማድረግ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት 6ኛ ፎቅ ነባሩ ህንፃ በግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ብር በባንክ ከፍያ ማዘዣ (ሲፒኦ) ማስያዝ አለባቸው።
ጨረታው 19/01/2019 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ የቴክኒካል መጫረቻ ሰነድ (ከላይ የተገለፁ ለቅድመ ግምገማ የሚያገለግሉ ዶክመንቶች የጨረታ ማስከበሪያ) ብቻ ከሰዓት 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት ነባሩ ህንፃ 6ኛ ፎቅ በሚገኘው በግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ይከፈታል፡፡ የፋይናንሺያል የመጫረቻ ሰነዶች የሚከፈቱት ቴክኒካል ተቀባይነት ላገኙት ብቻ ነው።
ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡
ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት
ስልክ ቁጥር 011-1-55-52-30 78
ድረ ገጽ (www.ethbspe.org)
Berhanena selam printing enterprise
አዲስ አበባ
ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት
