ድርጅታችን ሪዬስ ኢንጂነሪንግ አ.ማ. ከዚህ በታች የተገለጹትን ያገለገሉ የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ሪዬስ ኢንጂነሪንግ አ.ማ. ከዚህ በታች የተገለጹትን ያገለገሉ የኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ስለዚህ ማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 1000.00 (አንድ ሺ ብር) ከፍሎ በመግዛት በጨረታው መሳተፍ ይችላል።
|
ተ.ቁ |
የማሽኑ ዓይነት |
ሞዴል |
ሲሪያል ቁጥር |
|
1 |
Dozer |
D8R |
9EM06520 |
|
2 |
Dozer |
D8R |
9EM03502 |
|
3 |
Grader |
140 K |
SZL00657 |
|
4 |
Grader |
140 H |
5HM02899 |
|
5 |
Grader |
140 H |
XZH01984 |
|
6 |
Grader |
12 K |
SZP00205 |
ተጫራቾች ንብረቶቹን ሣሪስ አካባቢ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መሥሪያ ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ለሁለተኛ ጊዜ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ የሥራ ቀናት ዘወትር ጠዋት ከ3፡00 እስከ 10፡00 ሰዓት ድረስ በአካል ተገኝተው መመልከት ይችላሉ። ተጫራቾች የሚፈልጉትን ንብረት ሊገዙ የሚችሉበትን ዋጋ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ፎርም ላይ በመሙላትና እና ለጨረታ ማስከበሪያ ያቀረቡትን ዋጋ 5 በመቶ (5%) በCPO ብቻ በማስያዝ በድርጅቱ የፋሲሊቲ እና ጠቅላላ አገልግሎት ቢሮ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
ጨረታው በጋዜጣ ለሁለተኛ ጊዜ ከወጣበት ከ7 ተከታታይ የሥራ ቀናት በኋላ በሚኖረው የሥራ ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኩባንያው የሠራተኞች ክበብ ውስጥ ይከፈታል።
ማሳሰቢያ፡-
ኩባንያው ለገዢዎች የስም ማዛወር ሒደት እንዲረዳቸው አስፈላጊውን መረጃ ለመስጠት የሚተባበር ሲሆን ለመሣሪያዎቹ ከመንግስት የሚፈለገውን ማንኛውም ወጪ ገዢዎች መክፈል እንደሚኖርባቸው ለመግለጽ እንወዳለን። መሥሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም፡፡
ለበለጠ መረጃ:- ስልክ ቁጥር 0114-421133 የውስጥ መስመር 299
0114-403474/0973-380440
አድራሻ:- አዲስ አበባ ደብረዘይት መንገድ (ሣሪስ አካባቢ)
ሪዬስ ኢንጂነሪንግ አክስዮን ማህበር
