የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት የጥበቃ ስራ እና የግቢ ውስጥ እና አካባቢ አረንጓዴ ልማት እንክብካቤ በ“out source” በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት
- የጥበቃ ስራ እና
- የግቢ ውስጥ እና አካባቢ አረንጓዴ ልማት እንክብካቤ በ“out source” በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ነጋዴዎች መወዳደር ትችላላችሁ።
- ለ2017 ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ በዘርፉ ያላችሁ እንዲሁም የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈላችሁ፡፡
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መዝገባቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ለጥበቃ ስራ ከሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የድጋፍ ደብዳቤ ማምጣት የሚችል፡፡
- በግቢ ውስጥ እና አካባቢ አረንጓዴ ልማት እንከብካቤ ከአዳማ ከተማ የምግብ ዋስትና እና የስራ ፈጠራ ክህሎት/ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ ቢሮ የድጋፍ ደብዳቤ ማምጣት የሚችሉ እና በግቢ ውስጥና አካባቢ አረንጓዴ ልማት እንክብካቤ ስራ ላይ በ “IMX” የተደራጁ መሆን አለባቸው።
- ከዚህ በፊት ከአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በስነ-ምግባርም ሆነ በሌላ ምክንያት ደብዳቤ የተፃፈበት መወዳደር አይችልም፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የጨረታ ሰነድ ኮፒና ኦሪጅናል ለየብቻ በተለያየ ፖስታ ማሸግ አለባቸው።
- ስርዝ ድልዝ ያለው፣ የማይታይ የጨረታ ሰነድ ወይም የዋጋ ዝርዝር ተቀባይነት የለውም።
- ጨረታውን ካሸነፉ በኋላ የውል ማስከበሪያ ያሸነፉበትን ዋጋ 10% ማስያዝ የሚችሉ፡፡
- ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከኮሌጁ ግዥና ፋይናንስ የስራ ሂደት ክፍል ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ለእያንዳንዱ 200 (ሁለት መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ አለባቸው፡፡
- የጥበቃ ስራ ጨረታው የሚከፈተው በ23/10/2017 ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የግቢ ውስጥ እና አካባቢ አረንጓዴ ልማት እንከብካቤ ስራ ጨረታው የሚከፈተው በ23/10/2017 ከቀኑ 9፡30 ሰዓት ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የሚሞሉትን ዋጋ በመስሪያ ቤቱ ሰነድ ብቻ ላይ መሆን አለበት፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ 10,000 (አስር ሺህ) ብር በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ በ"CBE, CBO እና Sinqe" ባንክ ብቻ ማስያዝ የሚችል መሆን አለበት፡፡
መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0228123956 ደውለው መረዳት ይችላሉ፡፡
አዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ
