በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር-2 ስኳር ፋብሪካ (ሎት-1: የSingle Cab Pickup Toyota Land Cruiser መለዋወጫ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የብሔራዊ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር አግጨ/0012/ኦኩስፋ-2/2017
- በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር-2 ስኳር ፋብሪካ (ሎት-1: የSingle Cab Pickup Toyota Land Cruiser መለዋወጫ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ብቁ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ /CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የ90 ቀን የባንክ ዋስትና /BID BOND/ በመስኩ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ሥራ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፤ ተጫራቾች በመንግስት ግዥ የዕቃና አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር /suppler List/ ውስጥ መካተታቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት እና በተጨማሪ የበጀት ዓመቱን ታክስ ክሊራንስ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 (አስራ አምስት) ቀን ውሎ በአስራ ስድስተኛው ቀን ይከፈታል፡፡ የጨረታውን መክፈቻ ትክክለኛ ቀን በጨረታ ሰነዱ ላይ በግልጽ ተቀምጧል፡፡ ዘግይቶ የሚቀርብ የመጫረቻ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል፡፡
- ብቁ ተጫራቾች በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀውን የተሟላ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ቀን ድረስ ዘወትር በሥራ ሰዓት (ከሰኞ እስከ ዓርብ ከሰዓት በፊት ከ2፡00-6፡00፣ ከሰዓት በኋላ ከ7:00-10:30 እና ቅዳሜ ከሰዓት በፊት ከ2፡00-6:00) ቀጥሎ በተመለከተው አድራሻ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታው ሰነድ የሚሸጥበት ለውድድር የቀረበ ሰነድ የሚገባበትና የሚከፈትበት አድራሻ፡-
- በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ - አሞ ኩራዝ ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካ ማስተባበሪያ ቢሮ ቶታል ሶስት ቁጥር ማዞሪያ 300 ሜትር ከፍ ብሎ ተዘነአ ሆስፒታል አጠገብ የፈዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ህንጻ ግቢ ውስጥ፡
ስልክ ቁጥር - 0991149485 አዲስ አበባ ኢትዮጵያ 0938309160
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው በእያንዳንዳቸው ሎቶች የሚያስይዙት የጨረታ ማስከበሪያ በሲፒኦ (CPO) ብር 10,000.00 /አስር ሺህ ብር/ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሠከረለት የ90 ቀን ሲፒኦ (CPO) ወይም በቅድመ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /BID BOND/ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የዕቃው ርክክብ የሚፈፀመው አሞ ኩራዝ ቁጥር-2 ስኳር ፋብሪካ አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ቢሮ መጋዘን ነው።
- ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ60 ቀናት ነው፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ፀንቶ የመቆያ ጊዜ የጨረታው ዋጋ ፀንቶ ከሚቆይበት የመጨረሻ ቀን በኋላ ለ28 ቀናት ነው።
ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፈል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ኦሞ ኩራዝ ቁጥር-2 ስኳር ፋብሪካ በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ
Tel-0913369154/0940209464 አዲስ አበባ ግዥ ማስተባበሪያ ጽ/ቤትTel:
ሀይል ውሃ 0991149485/0938309160
አዲስ አበባ
በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ
የኦሞ ኩራዝ ቁጥር‐2 ስኳር ፋብሪካ አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
