በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስ/ር ኮሚሽን የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም በ2018 በጀት ዓመት በህግ ጥላ ስር ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ለምግብ አገልግሎት የሚሆን በሎት 1 ቅጭቅጭ የወጣለት የተበጠረ ሰርገኛ ጤፍ፣ በቆሎ፣ አተር፣ ፍርኖ ዱቄት፣ ባቄላ በሎት 2 አንበሳ ሻይ ቅጠል፣ ጨው፣ ስኳር፣ ዘይት በሎት 3 ጎመን ዘር፣ የተፈጨ በርበሬ፣ ቀይ ሽንኩርት፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ሞኮረኒ፣ ፓስታ፣ ሩዝ፣ ምስር ክክ አተር ክክ እና የተለያዩ ቅመማ ቅመም በሎት 4 የማገዶ የባህር ዛፍ እንጨት ከሐምሌ 1/11/2017 ዓ/ም እስከ ሰኔ 30/10/2018 ዓ/ም በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 01/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ማረሚያ ቤቶች አስ/ር ኮሚሽን የስልጤ ዞን የወራቤ ማረሚያ ተቋም በ2018 በጀት ዓመት በህግ ጥላ ስር ለሚገኙ የህግ ታራሚዎች ለምግብ አገልግሎት የሚሆን በሎት 1 ቅጭቅጭ የወጣለት የተበጠረ ሰርገኛ ጤፍ፣ በቆሎ፣ አተር፣ ፍርኖ ዱቄት፣ ባቄላ በሎት 2 አንበሳ ሻይ ቅጠል፣ ጨው፣ ስኳር፣ ዘይት በሎት 3 ጎመን ዘር፣ የተፈጨ በርበሬ፣ ቀይ ሽንኩርት፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ሞኮረኒ፣ ፓስታ፣ ሩዝ፣ ምስር ክክ አተር ክክ እና የተለያዩ ቅመማ ቅመም በሎት 4 የማገዶ የባህር ዛፍ እንጨት ከሐምሌ 1/11/2017 ዓ/ም እስከ ሰኔ 30/10/2018 ዓ/ም በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚህም መሠረት፡-
- ዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸውና በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመደቡ
- የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉና የንግድ ፍቃዳቸውን ያሳደሱ
- ቫት /VAT/ ተመዝጋቢ የሆኑ
- ጨረታው ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ለ60 ቀናት
- አሸናፊው ማንኛውንም ወጪ በራሱ ሸፍኖ ዕቃዎችን ወራቤ ማረሚያ ተቋም ቅጥር ጊቢ ማቅረብ የሚችል፤
- የጨረታው ማስከበሪያ 5000 (አምስት ሺህ ብር) በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ እውቅና ያለው የፋይናስ ተቋም የተረጋገጠ ቼክ፣ ሌተር ኦፍ ክሬዲት፣ ሲፒኦ ማቅረብ የሚችሉ
- በጨረታው አሸናፊ የሚሆን ታጫራቾች በአሸነፉባቸው ዕቃ አይነቶች 10% ማስያዝ የሚችል፤
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተከታታይ ባሉት 15 ቀናት ውስጥ ለሚወዳደሩበት አቅርቦት በዘርፉ የማይመለስ ብር 150 (አንድ መቶ ሃምሳ ብር) በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከግዥና ፋይናንስ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸውንና የመወዳደሪያ ሂሳባቸውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ አንድ ኦርጅናል እና አንድ ፎቶ ኮፒ እስከ 15ኛው ቀን 11፡00 ሰዓት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15ኛው ቀን ከቀኑ በ11፡00 ሰዓት ታሽጎ በ16ኛው ቀን በ3፡00 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። 16ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ታጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተቋሙ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 0911 80 41 23 መጠየቅ ይችላሉ።
የወራቤ ማረሚያ ተቋም
