ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ኤሌክትሮኒክስ (ኮምፒውተር፣ ፕሪንተር ፎቶ ኮፒ ማሽን እና ፕሮጀክተር) በሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ በማውጣት አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር NCB 0002/2017
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ኤሌክትሮኒክስ (ኮምፒውተር፣ ፕሪንተር ፎቶ ኮፒ ማሽን እና ፕሮጀክተር) በሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ በማውጣት አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት ተጫራቾች :-
- የዘመኑን ግብር የከፈሉና በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ
- የአቅራቢነት የምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸዉን የሚያረጋግጥ የተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ የተዘረዘረውን እያንዳንዱን ዋጋ ሞልተዉ / ፈርመው እና የድርጅቱን ማህተም በማድረግ ፋይናንሻል ኦርጂናል ዶክመንት አንድ እና ፋይናንሽያል ኮፒ አንድ ቴክኒካል ኦርጂናል አንድ እና ቴክኒካል ኮፒ አንድ ለየብቻ በማድረግ በሰም በታሸገ ኢንቬሎፕ አድርገው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እስከ 15ኛዉ ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ በድርጅቱ ግዥና ንብረት አስተዳደር አገልግሎት ክፍል በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታዉ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15ኛዉ ቀን በቀኑ 8፡00 ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በ 8፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል። 15ኛዉ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታዉ በሚቀጥለዉ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ ተዘግቶ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ (CPO) 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር ብቻ) ቴክኒካል ኦርጂናል ዶክመንት ውስጥ በማድረግ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የተዘጋጀዉን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ በ100.00 ብር ከድርጅቱ ግዥና ንብረት አስተዳደር አገልግሎት ክፍል ቀርበው መግዛት ይችላሉ።
- በጨረታዉ ሂደት አሸናፊዉ ድርጅት እቃዎቹን ቢሯችን ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይኖርበታል።
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
በስልክ ቁጥር 0912818102/0911995805 ደውለዉ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የድርጅቱ አድራሻ ሆሳዕና ከተማ ወደ ወልቂጤ መውጫ መንገድ ካቶሊክ ት/ቤት ጎን ላይ ነው
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ዲዛይንና ግንባታ ቁጥጥር ድርጅት ሆሳዕና
ኢትዮጵያ
