የሆሣዕና ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚዎች ለቀለብ አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች በሠንጠረዡ ውስጥ የተመለከቱትን የእህል አቅርቦቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለአሸናፊ ተጫራች ለመስጠት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር ሆማተ/29/2017
የሆሣዕና ማረሚያ ተቋም ለህግ ታራሚዎች ለቀለብ አገልግሎት የሚውል ከዚህ በታች በሠንጠረዡ ውስጥ የተመለከቱትን የእህል አቅርቦቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ በቅድሚያ ለአንድ ዓመት በሚቆይ የአቅርቦት ጊዜ ሆኖ፡- እንደ አስፈላጊነቱ በአቅራቢና ተቀባይ መካከል በሚደረገው የውል ስምምነት መሠረት እስከ ሶስት ዓመታት ለሚደርስ ጊዜያት ማለትም እስከ ሰኔ 2020 ድረስ እየተራዘመ የሚሰራ የግዥ ሂደት እንዳለ ታሳቢ በማድረግ፤ በማዕቀፍ ስምምነት በየወሩ ለሚያቀርቡ አቅራቢዎች በጨረታ አወዳድሮ ለአሸናፊ ተጫራች ለመስጠት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም-
|
ተ.ቁ |
የአቅርቦቱ አይነት |
መለኪያ |
የአቅርቦት መጠን |
የማቅረቢያ ጊዜ |
ርክክቡ የሚፈፀምበት ቦታ |
ለአቅርቦቱ በማዕቀፍ ስምምነቱ መሠረት በቅድሚያ ለ01 ዓመት ቆይታ ጊዜ ከ. . . እስከ |
|
01 |
ነጭ ሰርገኛ ጤፍ (100 ኪ/ግ) |
ኩንታል |
ከ25-50 ኩንታል |
ወር በገባ ከ25-30 |
ማረሚያ ተቋም |
ከ01/11/17-30/10/2018 |
|
02 |
ነጭ በቆሎ (100 ኪ/ግ) |
ኩንታል |
ከ100-170 ኩንታል |
ወር በገባ ከ25-30 |
ማረሚያ ተቋም |
ከ01/11/17-30/10/2018 |
|
03 |
ስንዴ (100 ኪ/ግ) |
ኩንታል |
ከ25-50 ኩንታል |
ወር በገባ ከ25-30 |
ማረሚያ ተቋም |
ከ01/11/17-30/10/2018 |
|
04 |
ባቄላ (100 ኪ/ግ) |
ኩንታል |
ከ15-25 ኩንታል |
ወር በገባ 25-30 |
ማረሚያ ተቋም |
ከ01/11/17-30/10/2018 |
|
05 |
ዛላ በርበሬ |
ኪ/ግ |
ከ50- 150 ኪ/ግ |
ወር በገባ 25-30 |
ማረሚያ ተቋም |
ከ01/11/17-30/10/2018 |
መመዘኛዎች
(01) በየመስኩ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያለው/ላት፤ የዘመኑን ግብር የከፈለ/ች፤ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያለው/ላት፤ ከማንኛውም ግብርና ታክስ ከፋይነት ነፃ እንዲሆኑ ከተፈቀደላቸው ድርጅቶችና ዩኒየኖችና ተመሳሳይ የንግድ ድርጅቶች በስተቀር የVAT 15% ተመዝጋቢ የሆኑና የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማስረጃ ሊያቀርቡ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
(02) ተጫራቾች ለሚጫረቱበት አቅርቦት በቀደምት የሥራ ዘመን ተጫርተው በማሸነፍ ለማረሚያ ተቋማት ወይንም ለሌሎች መንግስታዊና ሕዝባዊ ድርጅቶች ለ01 (አንድ) አመት እና ከዚያም በላይ ለሆነ ጊዜያት ያለእንከን ስለማቅረባቸው የመልካም ሥራ አፈፃፀም ደብዳቤ /ምስክር/ ወረቀት ማስረጃ ከሌሎች መጫረቻ ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ የሚችሉ፤
(03) አሸናፊው ተጫራች ለአቅርቦቱ ከላይ በተዘረዘሩት መስፈርቶች መሠረት በቅድሚያ ከሀምሌ 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ ለ12 /አስራ ሁለት/ ወራቶች በየወሩ ለማቅረብ ህጋዊ የውል ሰነድ የሚፈርምና በቅድሚያ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሸናፊው ነጠላ ዋጋ እንደተጠበቀ ሆኖ በየጊዜው የእህልም ሆነ የሌሎች ዕቃዎች ዋጋ ሲቀንስ ለመንግስት በመቀነስ ሲጨምር በማዕቀፍ ግዥዎች በተፈቀደው የዋጋ ማስተካከያ መመሪያ መሠረት ተጠቃሚ ሆኖ ለማቅረብ ፈቃደኛ የሚሆን፤
(04) ተጫራቾች ይህ ጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አየር ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ሆሣዕና ማረሚያ ተቋም ግዥና ፋይናንስ ንብ/አስ/ የሥራ ሂደት ቢሮ በአካል በመቅረብ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በነፃ መውሰድ የሚችሉ ሲሆን፤ የጨረታ ማስከበሪያን በሚመለከት ለሰብል ዓይነቶች ከጠቅላላ አቅርቦት ዋጋ 2% የብር 30,000 /ሰላሳ ሺህ/ CPO /ተመሳሳይ/ ሰነድ በማሰራት ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
(05) ተጫራቾች:- ይህ ጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አሥራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት የእያንዳንዱን እህል የአንዱን ኩንታል እንዲሁም ዛላ በርበሬ በኪሎ ግራም ነጠላ ዋጋ ከነማስረጃው ኰፒዎች ጋር በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ አዘጋጅተው ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
(06) ተጫራቾች የእህል ዓይነቶችን ናሙና የማቅረብ ግዴታ እንዳለባቸው መዘንጋት የለባቸውም
(07) ጨረታው በ15ኛው ቀን ከቀኑ 11፡30 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች /ህጋዊ/ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 16ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት በማረሚያ ተቋሙ ቅጥር ግቢ አዳራሽ /ቢሮ የሚከፈት መሆኑን ስንገልጽ ዕለቱ የበዓላት/ የዕረፍት ቀን ከሆነ በማግስቱ በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እያሳሰብን መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።
የሆሣዕና ማ/ተቋም
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0926200823 (0912052832) ደውሎ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የሆሣዕና ማረሚያ ተቋም
