የሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ ለ2018 ዓ/ም ለክለቡ ስፖርተኞች በአንድ ሆቴል ውስጥ የሆነ የአልጋ ኪራይ እና የምግብ መስተንግዶ በጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ ለ2018 ዓ/ም ለክለቡ ስፖርተኞች በአንድ ሆቴል ውስጥ የሆነ የአልጋ ኪራይ እና የምግብ መስተንግዶ በጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት፡-
ከዚህ በታች ተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ አቅራቢዎች መወዳደር ይችላሉ።
- በሥራ መልኩ ሕጋዊ የታደሠ ንግድ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣ የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑ።
- የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለተመዘገቡ ጨረታዎች የጨረታ ማስከበሪያ 50,000 (ሃምሳ ሺህ) ብር በባንክ የተረጋገጠ (የተመሰከረ) ሲፒኦ (CPO) ወይም ቢድ ቦንድ ከጨረታ ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ሰነዱን ከሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ ቢሮ በመቅረብ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከመጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 /ለአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናትን በመጠቀም ብር 1,000.00 /አንድ ሺህ/ ብር በመክፈል መግዛት ይቻላል።
- የተወዳዳሪ ሆቴል ደረጃ በባሕልና ቱሪዝም ሰርተፍኬት የተሰጠው ከባለ 3 ኮኮብ በላይ የሆነ መሆን አለበት፤ ማስረጃውንም አያይዞ ኮፒ ማቅረብ አለበት።
- የጨረታ ሰነዱ በሰም ለየብቻቸው በታሸገ ኤንቨሎፕ አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ኮፒ ፋይናንሻል በማያያዝ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተከታታይ ቀናትን በመጠቀም በሀዋሳ ከተማ ስፖርት ከለብ ፋይናንስ ቢሮ አርተፊሻል ሜዳ ቢሮ ቁጥር 1 ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበትም ሆነ ባልተገኙበት 4፡00 ሰዓት በቢሮ ቁጥር 1 ይከፈታል። ይህ ቀን ቅዳሜ ወይም እሁድ ከሆነ እንዲሁም የበዓላት ቀን ከሆነ በተመሣሣይ ሰዓት በሚቀጥለው የሥራ ቀን ጨረታው ይከፈታል።
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ስልክ ቁጥር 046-212-4176
የሀዋሳ ከተማ ስፖርት ክለብ
