የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በ2018 በጀት ዓመት የሚገለገልባቸውን እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኢ.ሚ.ኔ.ብ.ግ.ጨ.001/2017
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በ2018 በጀት ዓመት የሚገለገልባቸውን እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በዚህም መሠረት፡-
- የዩፒስ /ups ግዥ
በግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት የሚፈልግ በመሆኑ በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
- በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉና የገቢዎች ክሊራንስ ያላቸው።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችሉና፣ በግዥ አቅራቢነት የተመዘገቡ።
- ተጫራቾች በሚያቀርቡት እያንዳንዱ ሰነድ እና ፖስታ ላይ የድርጅቱን ማህተምና ፊርማቸውን ማኖር ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት አጠቃላይ ዋጋ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 400,000.00 በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የሚያሳይ የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ቢሮ ቁጥር 6 የማይመለስ ብር ለሰነድ መግዣ 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 28 መግዛት ይችላሉ።
- ጨረታው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 ይከፈታል። ሆኖም ግን የተጫራቾች አለመገኘት ጨረታውን ከመክፈት አያግደውም። የመክፈቻው ዕለት በዓል/ዕረፍት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን ዋናውንና ኮፒውን / ቴክኒካል ኦርጅናልና ኮፒ፣ ፋይናንሻል ኦርጅናልና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
- በአንዱ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ የተከለከለ ነው፡፡
- በጨረታ ያሸነፈ ተጫራቾች ከመ/ቤታችን ጋር ጨረታውን እንዳሸነፈ ካወቀበት ጊዜ አንስቶ በ15 ቀናት ውስጥ በሲፒኦ የጠቅላላ ዋጋውን 10% በማስያዝ ውል መዋዋል ይኖርበታል።
- ተቋሙ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ
የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርከ 5 ኪሎ ቅድስት ማርያም ቤ/ክርስቲያን ከማኅበረ ቅዱሳን ጀርባ ያለው ህንፃ።
ለበለጠ መረጃ ስልክ፡- 0111 116382 መደወል ይችላሉ።
አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ
