በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የማልጋ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት በኩል በወተራ-ረሳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግቢ ውስጥ ያለውን ባህር ዛፍ፤ የተፈጥሮ ጽድ፣ የፈረንጅ ጽድ፣ የሀገር በቀል እንጨት፣ ድክርስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የማልጋ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት በኩል በወተራ-ረሳ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ግቢ ውስጥ ያለውን ባህር ዛፍ፤ የተፈጥሮ ጽድ፣ የፈረንጅ ጽድ፣ የሀገር በቀል እንጨት፣ ድክርስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የተጨማሪ እሴት ታከስ ተመዝጋቢ የሆኑ የአቅራቢነት ምዝገባ ወረቀት ያላቸውና የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ለ21 /ሀያ አንድ/ ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ዋጋ የተሞላበትን 1 ኦሪጅናልና 1 ፎቶ ኮፒ የጨረታ ሰነድና የጨረታ ማስከበሪያ (CPO) 10,000 /አስር ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ዋስትና በፖስታ ለየብቻቸው በማሸግ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታውን ሰነድ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን አንስቶ ለ21 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በማልጋ ወረዳ ግዥ ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 14 በመክፈል መውሰድ ይችላሉ። በ22ኛው ቀን 4፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ሰነዳቸውን አሽገው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በዚሁ ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች የተጫረቱበትን ንብረት በ10 /አስር/ ቀናት ውስጥ ማንሳት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው አለመገኘታቸው ጨረታውን ከመከፈት አያግደውም፡፡
- የጨረታ አሸናፊው የጨረታ ውጤት ሲታወቅ የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ የጨረታ ዋጋ 10% CPO በባንክ በተረጋገጠ ዋስትና ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የስራ ቀን ላይ ካልዋለ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተገለጸው ቦታና ሰአት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ማሳሰቢያ፡- አሰሪው መ/ቤት የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የማልጋ ወረዳ ፋይ/ኢኮ/ል/ጽ/ቤት
