ሬች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በበጀት ዓመቱ እቅድ መሰረት በድርጅቱ ለታቀፉ ተማሪዎች የሚሆን የመማሪያ ቁሳቁስ ደብተር፣ ቢክ እስክሪብቶ፣ የቢሮ የጽሕፈት መሳሪያዎች እና የሥልጠና መገልገያ ቁሳቁሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ሬች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ያልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በበጀት ዓመቱ እቅድ መሰረት በድርጅቱ ለታቀፉ ተማሪዎች የሚሆን የመማሪያ ቁሳቁስ ደብተር፣ ቢክ እስክሪብቶ፣ የቢሮ የጽሕፈት መሳሪያዎች እና የሥልጠና መገልገያ ቁሳቁሶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
መለኪያ |
ብዛት |
ምርመራ/ አስተያየት |
|
1 |
ደብተር (ሲነር ላይን) ባለ 50 ገጽ |
በቁጥር |
10,000.00 በላይ |
ያልተለበደ |
|
2 |
ቢክ እስክሪብቶ ኬኒያ አንደኛው |
በቁጥር |
5,000.00 በላይ |
ኦርጅናል |
|
3 |
የሥልጠና ጽሕፈት መሳሪያ ዕቃዎች |
በቁጥር |
|
የተለያዩ የጽሕፈት መሳሪያዎች |
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ቢያንስ የሚከተሉትን ማሟላት ይኖርባቸዋል።
- የዘመኑ የታደሰ የንግድና የታደሰ የዋና ምዝገባ ፈቃዳቸውን፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ሰርተፍኬት፣ በጨረታ እንድትሳተፉ ለዘመኑ በጀት ዓመት ብቻ የሚያገለግል የምስክር ወረቀት እና ቲን ሰርተፍኬት ፎቶ ኮፒውን በማያያዝ የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ሰባት የሥራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ2፡30 – 6፡30 እና ከሰዓት 7፡30 -11:30 ከላይ የተዘረዘሩትን መረጃዎች ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በማያያዝ ዲላ በሚገኘው ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ ጽ/ቤት ሂሳብ ክፍል በመምጣት መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒውን በሰም በታሸገ ኢንቬሎፕ (ፖስታ) የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ 10,000.00 ብር (አስር ሺህ ብር) ሲፒኦ በሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ ስም ተሰርቶ በኦርጅናል የጨረታ ሰነድ ውስጥ በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ከሰባተኛው /7ኛው/ ቀን በኋላ ባለው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 6፡30 ድረስ ለዚህ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው በዕለቱ ከሰዓት 8፡00 ሰዓት ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ አዳራሽ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 046-331-0049/046-331-31-45 ዘወትር በሥራ ሰዓት ደውሎ መጠየቅና መረዳት ይቻላል።
አድራሻ፡ ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ ዲላ ከተማ ከዲላይት ኢንተርናሽናል ሆቴል 100 ሜትር ገባ ብሎ፡፡
ሪች ዘ ኒዲ ኢትዮጵያ
