በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት በጌዴኦ ዞን የዲላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ር ዲቪዥን ከሐምሌ ወር 2017 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሕግ ታራሚዎች የምግብ ቀለብ የሚውል እህል፣ የባልትና ውጤቶች የምግብ አላቂ ዕቃዎች እና ለምግብ ማብሰያ የሚውል የማገዶ እንጨት ግዥ ለመፈጸም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ ጨረታ ቁጥር 03/2017
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት በጌዴኦ ዞን የዲላ ማረሚያ ፖሊስ ተቋም ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ር ዲቪዥን ከሐምሌ ወር 2017 ዓ.ም እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሕግ ታራሚዎች የምግብ ቀለብ የሚውል እህል፣ የባልትና ውጤቶች የምግብ አላቂ ዕቃዎች እና ለምግብ ማብሰያ የሚውል የማገዶ እንጨት ግዥ ለመፈጸም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- 1ኛ. በማሽን የተፈጨ የስንዴ ዱቄት/ፍኖ
- 2ኛ ያልተቆላ የባቄላ ክክ
- 3ኛ የባልትና በርበሬ
- 4ኛ ቃሪያ
- 5ኛ የምግብ ጨው
- 6ኛ የምግብ ዘይት
- 7ኛ የዕቃ ማጠቢያ ሽቦ
- 8ኛ መሳቢያ
- 9ኛ ሻይ ቅጠል
- 10ኛ ሻይ ቅመም
- 11ኛ የአቢስት ማጣሪያ ወንፊት
- 12ኛ የማገዶ እንጨት መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ጨረታው የሚካሄደው የሥራ ቋንቋ አማርኛ ሲሆን ፤በሚወዳደሩበት የንግድ ሥራ ዘርፍ ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ፣የግብር ከፋይነት ማስረጃ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉና ፈቃዳቸውን ያሳደሱ፣ በተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ ፣በጨረታ መወዳደር የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤ ከመንግሥት ገቢዎች ጽ/ቤት ማቅረብ የሚችሉ እና በአቅራቢነት ዝርዝር ለመመዝገባቸው ማስረጃ የሚያቀርቡ ተጫራቾች በሚወዳደሩበት የንግድ ሥራ መስክ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10000.00 /አስር ሺህ/ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም ሕጋዊ ጥሬ ገንዘብ ማቅረብ የሚችሉና በጨረታ የተጠቀሱ መሥፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለአሥራ አምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን፤ የማይመለስ የኢትዮጵያ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል የጨረታውን ሰነድ በየሎት የተዘጋጀውን ከዲላ ማረሚያ ተቋም ግዥ ፋይ/ን/አስ/ር ዲቪዥን ገዝተው ከሞሉ በኋላ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ አሥራ አምስተኛው ቀን 5፡45 ሰዓት የጨረታ ሣጥን ከታሸገ በኋላ በእለቱ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዲላ ማረሚያ ተቋም ይከፈታል። እለቱ የስራ ቀን ባይሆን በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል። ተጫራቾች የጨረታ ሠነዳቸውን ወደ ጨረታ ሣጥን አስገብተው በከፈታ እለት የማይገኙ ቢሆን እንኳ ጨረታው ይከፈታል፡፡አንዱ ተጫራጭ ባቀረበው ዋጋ ላይ ተንተርሰው ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፡፡የጨረታ አሸናፊ ማሸነፉ ከተገለጸ ጊዜ ጀምሮ የስድስት ወሩን አቅርቦት ዋጋ 10 0/0 የውል ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ አቅርበው ውል መፈጸም አለባቸው፡፡ አሸናፊዎች አሸናፊነታቸው እንደተገለጸ ውል የማይፈጽሙ ከሆነ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ አይመለስም፡፡ የጨረታውን ዝርዝር በጨረታ አፈጻጸም መመሪያ ላይ የተገለጸ ስለሆነ በይበልጥ ተቀባይነት ያለው ሠነድ በመሆኑ ማንበብ ይኖርባቸዋል።
መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በመሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 046-331-3085/046-331-7754 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
የዲላ ማረሚያ ተቋም ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ር ዲቪዥን
ዲላ
