በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሰት ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በጎፋ ዞን የሣውላ ማረሚያ ተቋም በ2018 በጀት ዓመት የጽህፈት መሣሪያ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሰት ማረሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በጎፋ ዞን የሣውላ ማረሚያ ተቋም በ2018 በጀት ዓመት የጽህፈት መሣሪያ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ሰለሆነም ከዚህ በታች መስፈርቱን የሚታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- በዘርፉ ንግድ ፍቃድ ያለው።
- የዘመኑን ግብር የከፈለ።
- የግብር መለያ /Tin/ ቁጥር ያለው።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የቫቲ ተመዝጋቢ የሆነ።
- በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡና የምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ።
- የጨረታ ማሰከበርያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ ፣ በCpo ፣ በጥሬ ገንዘብ ለጽህፈት መሣሪያ 15,000 ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ከ1 እስከ 5 የተጠቀሰውን ማስረጃዎችን እና የማጫረቻ ሠነድ ኦርጅናልና ኮፒ በተለያዩ ፖስታ ውሰጥ በማሰገባት በአንድ እናት ፖሰታ ውሰጥ በታሸገ ኤንቨሎፕ ለዚህ በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን በመንግስት የሥራ ሰዓት ማስገባት አለባቸው።
- የጨረታ ማስታወቂያ ከታወጀበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ ለ15 ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን የጨረታ ሣጥን 16ኛዉ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው ይከፈታል፡፡ ዕለቱ ቅዳሜ ፣ እሑድ እና የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው ቀን በመንግሰት ሥራ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የሣዉላ ማረሚያ ተቋም የግዥ ፋ/ን/አስ/ር ደጋፊ ሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 9 በመቅረብ ጨረታ የማይመለሰ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሠነድ መግዛት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ በፊት የጽህፈት መሣሪያ ማለትም የኮምፒውተር ወረቀቶች፣ እስክሪብቶች እና የደብተሮች ናሙና መቅረብ አለበት፡፡
- ተጫራቾች ዕቃውን በራሳቸዉ ወጪ እስከ ሣውላ ማረሚያ ተቋም አምጥተው ማስረከብ አለባቸው።
- የጨረታው አሸናፊዎች ሆነው የተገኙ ተጫራቾች የዕቃዎችን አጠቃላይ ዋጋ በ10% በባንክ የተረጋገጠ ቼክ ወይም /Cpo/ የውል ማስከበርያ በማስያዝ ከሳዉላ ማረሚያ ተቋም ግዥ ፋ/ን/አስ/ር ደ/ሥራ ሂደት ጋር የዉል ስምምነት መፈፀም ይጠበቅባቸዋል፡
- በሌሎች ተጫራቾች ዋጋ ላይ ተንተርሶ መወዳደር ተቀባይነት የለውም፡፡
- ማረሚያ ተቋሙ የተሻለ አማራጭ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ ማብራርያ ስልክ ቁጥር 0467770041/0916479909/
የሣውላ ማረሚያ ተቋም የግዥ ፋ/ን/አስ/ር ደጋፊ ሥራ ሂደት
