ፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ ለተጎዱ መኪናዎች ማቆያ የሚሆን ቦታን (Recovery Yard) በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የሪከቨሪ ቦታ ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
ፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ ለተጎዱ መኪናዎች ማቆያ የሚሆን ቦታን (Recovery Yard) በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም ማንኛውም መስፈርቱን የምታሟሉ እና መሸጥ የምትልጉ ህጋዊ የባለቤትነት ማረጋገጫ ያላችሁ ባለይዞታዎች ከዚህ በታች በተገለፀው ዝርዝር መሰረት እንድትወዳደሩ ተጋብዛችኋል።
የሚፈለገው ቦታ ዝርዝር መስፈርቶች፤
|
ተ.ቁ |
ዝርዝር መግለጫ |
ተፈላጊ መስፈርት |
|
1 |
የቦታው ጠቅላላ ስፋት |
ከ 17000-12000 |
|
2 |
ቦታው የሚፈለግበት አካባቢ |
አካባቢ አዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ሆኖ አቃቂ ቃሊቲ ቦሌ ቡልቡላ ለቡ፣ ሃና ማርያም፣ ገላን ኮንዶሚኒየም፤ ቱሉዲምቱ አከባቢዎች መሳተፍ ይቻላል። |
|
3 |
የባለቤትነት ማረጋገጫ |
የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ከማናኛውም የባንክ እና ሌላ ዕዳና እገዳ ነፃ የሆነ፣በቀላሉ ስም ማዛወር የሚችልና ምንም አይነት የህግ ክርክር የሌለበት |
|
4 |
ተፈላጊ ዶክመንት |
በጨረታ ሰነዱ ላይ በተመለከተው ሁኔታ |
|
5 |
የቦታው የአገልግሎት አይነት |
ለጋራዥ ለማከማቻ (Storage) እና ሪከቨሪ አገልግሎት የተፈቀዴ |
|
6 |
ቦታው የሚገኝበት ሁኔታ |
ለአባድ መኪናዎች መተላለፊያነት የሚያገለግል የውስጥ ለውስጥ መንገድ ምቹ የሆነ እና ከዋናው አስፓልት ያልራቀ |
|
7 |
ለመሸጥ ፍላጎት ያላችሁ ለዚሁ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከዋናው መ/ቤት 3ኛ ፎቅ ፋይናንስ እና አካውንቲንግ መምሪያ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፍል መውሰድ ትችላላችሁ። |
|
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 20 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ቦሌ ድልድይ የቀድሞው ብራስ ሆስፒታል ፊት ለፊት በሚገኘው ፀሐይ ኢንሹራንስ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት 1ኛ ፎቅ ለዚሁ በተዘጋጀው ጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይቻላል።
- ተጫራቾች ያስገቡትን የጨረታ ሰነድ መስከረም 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ተዘግቶ በዚያው ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ የሚከፈት ሲሆን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተጨማሪ መረጃ ፀሐይ ኢንሹራንስ ኢማ ዋና መስሪያ ቤት 1ኛ ፎቅ በአካል በመቅረብ
ወይም
በስልክ ቁጥር 011-1-11 96 49 ደውለው ማግኘት ይችላሉ።
