በአብክመ የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የመኪና መለዋወጫ እቃዎች ግዥ ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በአብክመ የጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ የመኪና መለዋወጫ እቃዎች ግዥ ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል።
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የሚመለከተው የንግድ ፈቃድ ያላቸው።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው።
- የግዥው የብር መጠን 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለበት ለዚህም ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።
- ተጫራቾች ከ1 እስከ 3 የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200 ብር በመክፈል ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ዘወትር በስራ ሰአት ቢሮ ቁጥር 19 መግዛት ይችላሉ። በ16ኛው ቀን 3፡35 ታሽጎ በ4፡00 ሰዓት ይከፈታል። ነገር ግን ቀኑ በዓል ከሆነ የሚቀጥለው ቀን ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሞሉትን ጠ/ዋጋ 1.5% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በአማርኛ የተተረጎመ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማቅረብ አለበት። በጥሬ ገንዘብ የሚያስይዙ ከሆነ በውስጥ ገቢ ደረሰኝ መቁረጥ አለበት።
- ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ ጎ/መ/ት/ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር G1 በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0581121634 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የጎንደር መም/ትምህርት ኮሌጅ
