የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን Desktop for Standard Use /Core i5, Desktop for Advanced tasks /Core i7, Laptop Core i5, Laptop Core i7, Printer, Photocopy Machine, UPS, Color printer & Computer Mouse ተዛማጅ እቃዎች ግዥ በጨረታ መለያ ቁጥር ፌ.ቤ.ኮ/ብግጨ/ዕቃ/01/11/2017 ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ፌ.ቤ.ኮ/ብግጨ/ዕቃ/01/11/2017
- የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን Desktop for Standard Use /Core i5, Desktop for Advanced tasks /Core i7, Laptop Core i5, Laptop Core i7, Printer, Photocopy Machine, UPS, Color printer & Computer Mouse ተዛማጅ እቃዎች ግዥ በጨረታ መለያ ቁጥር ፌ.ቤ.ኮ/ብግጨ/ዕቃ/01/11/2017 ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- ለኮርፖሬሽኑ አገልግሎት የሚያገለግል የኮምፒውተር እና ተዛማጅ እቃዎች ግዥ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ቴክኒካል ሰነዳቸውንና ዋጋቸውን በተለያዩ በታሸጉ ኤንቨሎፖች ማቅረብ አለባቸው፡፡
|
ተ.ቁ |
የዕቃ ዝርዝር |
የጨረታ ማስከበሪያ |
|
1 |
የኮምፒውተር እና ተዛማጅ እቃዎች |
50,000.00 |
- ጨረታው የሚከናወነው በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ሥነ-ሥርዓትና ይኸንኑ አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የፈዴራል ቤቶች ኮርፓሬሽን የግዥ መመሪያ መሠረት ሲሆን ከሚፈለገው የኮምፒውተር እና ተዛማጅ እቃዎች ግዥ ጋር የተዛመደ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የግብር ከፋይ ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን ይኖርበታል፡፡
- የተሟላ የጨረታ ሰነዶችን ማንኛውም ፍላነት ያለው ተጫራች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ለገሀር በሚገኘው የኮርፓሬሽኑ ዋና መ/ቤት ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201 በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 201 ለዚሁ ታሽጎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው በመጀመሪያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ወይም መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ እንዲያቀርቡ ሆኖ ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ በባንክ በተመሰከረለት የባንክ ዋስትና ወይም ሲ.ፒኦ በፈዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው:: ከጨረታው መክፈቻ ዕለትና ሰዓት ዘግይቶ የቀረበ የጨረታ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል፤ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡15 ሰዓት በኮርፖሬሽኑ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክተር 1ኛ ፎቅ በሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ
በስልክ ቁጥር፡- 011-85-53-617 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
ዌብሳይት: - Website WWW.agh.gov.et
የፖ.ሣ.ቁ/P.O.Box:- 299
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን
