የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሲዳማ ሪጅን ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል የስቴሽነሪ ግዥ ለመፈፀም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የሚወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር ኢ/ኤ/አ/ሲ/ሪ/ግ/ጨ/001/2018
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሲዳማ ሪጅን ጽ/ቤት ለቢሮ አገልግሎት የሚውል የስቴሽነሪ ግዥ ለመፈፀም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ዝርዝሩም እንደሚከተለው ነው፡-
|
ተ/ቁ |
የእቃው አይነት |
መለኪያ |
ብዛት |
|
1 |
የኮምፒውተር ወረቀት |
ካርቶን |
1000 |
|
2 |
ቦክስ ፋይል |
በቁጥር |
2500 |
|
3 |
ስቴፕለር ሽቦ ትንሹ |
ፖኬት |
200 |
|
4 |
አግራፍ ትልቁ |
ፖኬት |
300 |
|
5 |
ፖንቸር / ወረቀት መብሻ ትንሹ |
በቁጥር |
42 |
|
6 |
የመዝገብ ቤት ፋይል አቃፊ ባለገመድ |
በቁጥር |
1360 |
- ተጫራቾች የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ የሚያቀርቡና በመስኩ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው፣ የተጨማሪ አሴት ታክስ ተመዝጋቢ፣ እንዲሁም በኤጀንሲው ድረ-ገፅ http://www.ppa.gov.et ውስጥ የተመዘገቡ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሠነድ ለመግዛት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ገንዘብ ብር 400.00 (አራት መቶ ብር) በኢ/ኤ/አገ/ሲዳማ ሪጅን ጽ/ቤት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000068760047 በማስገባትና የባንክ ደረሰኙን ከታች በሚገኘው አድራሻ በማቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡ ሐዋሳ ከተማ መናኸሪያ ክፍለ ከተማ በአሮጌው መነሃሪያ ጎን በሚገኘው የድርጅቱ ሕንጻ የኢ/ኤ/አገ/ሲዳማ ሪጅን ፋይናንስና ቁጥጥር ቢሮ ቁጥር 405
- ተጫራቾች ብር 36,000 (ሰላሳ ስድስት ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመረኮዘ የባንክ ጋራንቲ (Bid Bond) ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን እና በተ/ቁ 1 የተጠቀሱ ማስረጃዎችን በታሸገ ኤንቨሎፕ ኮፒና ኦርጅናል በማለት እስከ ተጠቀሰው የጨረታው መዝጊያ ቀን መስከረም 26/2018 ዓ.ም 9፡00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተ/ቁ 2 ላይ በተገለጸው አድራሻ በመቅረብ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት በዚሁ ቀን መስከረም 26/2018 ዓ.ም በ9:00 ሰዓት ይሆናል፡፡
- ጽ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጫራቾች መረጃ ከፈሰጉ በስልክ ቁጥር 0462201970 መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሲዳማ ሪጅን ጽ/ቤት
