የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የስንዴ ምርት ግዥ በዘርፉ የተሰማሩ አቅራቢዎችን በጨረታ በማወዳደርግዥውን መፈጸም ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ ኢንሥኮ/ብግጨ 01/2018
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን የስንዴ ምርት ግዥ በዘርፉ የተሰማሩ አቅራቢዎችን በጨረታ በማወዳደርግዥውን መፈጸም ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታ ላይ መወዳደር የሚፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መመዘኛዎች ማሟላት አለባቸው።
1. የሰንዴ ምርት ግዥ አጠቃላይ ብዛት 500 ሺህ ኩንታል
የሚፈለገው የጥራት ደረጃ፡-
- የምርት ዘመን 2016/2017
- ከእርጎነትና አስመት ነፃ የሆነ፣
- የእርጥበት ልክ ከ13% ያልበለጠ፤
- ሕይወት ካለው ተባይ ነፃ የሆነ፤
- የባአድ ስሪት መጠን ከ2% ያልበለጠ፤
- የቀጨጨ፣ የተሰባበረ፣ መልኩን የቀየረ በብርድ የተመታ ከ6% ያልበለጠ፤
- ጠቅላላ የጥራት ጉድለት ከ8% ያልበለጠ፤
የማቅረቢያ ቦታ፡- አዲስ አበባ፣ አዳማ እና ድሬዳዋ በኮርፖሬሽኑ መጋዘኖች
2. ተጫራቾች በዘርፉ የ2017 በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ፈቃድ /ጨረታው እስከሚከፈትበት ቀን ድረስ ሊያገለግል የሚችል የንግድ ስራ ፈቃድ፤ የንግድ ምዝገባ ምስከር ወረቀት፤ የአቅራቢነት ምዝገባ የምስከርወረቀት፤ በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት የተሰጠ ወቅታዊ ከሊራንስ፤ የተጨማሪ እሴት ታከስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት እና የግብር ከፋይ ምዝገባ ስርተፊኬት (TIN/ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። እነዚህ ሰነዶች በቴከኒካል ፕሮፖዛል ፖስታ ውስጥ ታሽገው መቅረብ ይኖርባቸዋል።
3. ተጫራቾች ከላይ የተገለጹትን ሰነዶች ከጨረታ ሰነድ ማቅረቢያው ቀነ ገደብ በፊት ማቅረብ አለባቸው።
4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመከፈል ከመስከረም 7 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከ2:00 -6፡00 ሰዓት እንዲሁም ከሰዓት ከ7፡00-11፡00 ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜ ከ2፡00-6፡30 ሰዓት ድረስ ማዕከል ግዥ ዋና ክፍል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
5. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን እስከ ጨረታው መዝጊያ ዕለት እስከ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡30 ሰዓት ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
6. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር 500,000.00 /እምስት መቶ ሺህ ብር/ በሲፒኦ፣ ጥሬ ገንዘብ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም አሰርተው ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው። ኢንሹራንስ ቦንድና ቼከ ተቀባይነት የላቸውም። የጨረታ ማስከበሪያው በቴክኒካል ፕሮፖዛል ፖስታ ውስጥ ወይም ለብቻው ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል።
7. የቴከኒክ ሰነድ እና የፋይናንሻል ሰነድ በፖስታ በማሸግና ኮፒ እና ኦሪጅናል የፋይናንሻል እንዲሁም የቴከኒካል ሰነድ ኮፒዎችን ለየብቻ በፖስታ በማሸግ በአንድ ላይ በትልቅ ፖስታ ሁሉንም ፖስታዎች በማድረግ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም በ4፡30 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ዋናው መ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል። አድራሻ ከታች ተገልጿል።
8. ተጫራቾች የስንዴ መሸጫ ዋጋ በ3ቱ ማቅረቢያ ቦታዎች ለየብቻ ተለያይቶ ዋጋ ማቅረብ አለባለቸው።
9. አሸናፊው ድርጅት የውል ማስከበሪያ መጠን ለአሸነፉበት የስንዴ ምርት ጠቅላላ ዋጋ 10 ፐርሰንት በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም እሰርተው ውሉን የሚፈጽሙ ይሆናል።
10. ኮርፖሬሽኑ ጨረታውን በከፊልም ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ለማንኛውም ማብራሪያ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 011-4-18-73-45/ 011-4-66-93-36 በመደወል መጠየቅ ይቻላል። ስድራሻ፡- ደብረዘይት በሚወስደው መንገድ በቅሎ ቤት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን
