ቦሌ ማተሚያ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ቦንድ 70 ግራም 70X100 ወይም 61X86 ወረቀት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የሀገር ውስጥ የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
ቦሌ ማተሚያ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ቦንድ 70 ግራም 70X100 ወይም 61X86 ወረቀት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- ተጫራቾች፡- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የቫት ተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት፤ የንግድ ሰርተፊኬት እና ሌሎችም የህጋዊነት ማረጋገጫ ሰነዶችን ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በቅድሚያ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር/ ቢሮ ቁጥር 101 በመክፈል ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ድረስ ቦሌ መንገድ ከቶታል ነዳጅ ማደያ ዝቅ ብሎ በሚገኘው ቢሮአችን መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የዋጋቸውን 2%፣ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ /ሲፒኦ/ በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ቴክኒካል እና ፋይናንሺል ሰነዶችን በአንድ ፖስታ አሽገው ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከግዥ ክፍል በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ያስገባሉ፡፡
- ተጫራቾች ለጥራት ሙከራ ይሆን ዘንድ በቂ የሆነ ናሙና ከሰነዶቻቸው ጋር አብሮ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው።
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው 15ኛው ቀን ከረፋዱ 3፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ በ3፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኘበት በማህበሩ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ ሌላ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡-
ቦሌ ማተሚያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር
ስልክ ቁጥር 01115 15 50 05/0115 51 88 72
ፋክስ 0115 51 86 96
ፖ.ሳ.ቁ. 2365
ቦሌ መንገድ ከቶታል ነዳጅ ማደያ ዝቅ ብሎ
የቦሌ ማተሚያ ኃ.የተ.የግ.ማህበር
