ለፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ስር የሚገኙ ነባር ቤቶችን በጨረታ መለያ ቁጥር ፌ.ቤ.ኮ/ብ.ግ.ጨ/አገ.04/01/2018 መግዛት የሚፈልጉ ተጫራቾችን አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የ4ኛ ዙር ቤቶች ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር፡- ፌ.ቤ.ኮ/ብ.ግ.ጨ/አገ/04/01/2018
- ለፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ስር የሚገኙ ነባር ቤቶችን በጨረታ መለያ ቁጥር ፌ.ቤ.ኮ/ብ.ግ.ጨ/አገ.04/01/2018 መግዛት የሚፈልጉ ተጫራቾችን አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
- ኮርፖሬሽኑ ለሚያከናውነው የቤቶች ሽያጭ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን እና የመወዳደሪያ ዋጋ በአንድ ፖስታ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው የሚከናወነው በብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ሥነ-ሥርዓትና ይኸንኑ አስመልክቶ በኢትዮጵያ ፈዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የፈዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን መመሪያ መሰረት ነው።
- የተሟላ የጨረታ ሰነዶችን ማንኛውም ፍላጎት ያለው ተጫራች ከመስከረም 23 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ቅዳሜን ጨምሮ ባሉት 21 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከ2፡00 እስከ 11፡00 ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 6፡00 ድረስ የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በካሽ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ለገሐር በሚገኘው በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት እንዲሁም በቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በኩል በአካል በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራች የጨረታ ሰነዶቻቸውን በኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት በሚገኘው ዋና የመሰብሰቢያ አዳራሽ 1ኛ ፎቅ ለዚሁ ታሽጎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ከጥቅምት 16 እስከ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት ሶስት ቀናት እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ እንዲያቀርቡ ሆኖ ተጫራቾች ማስከበሪያ ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በሁኔታዎች ላይ ለጨረታ ያልተመሰረተ ሲ.ፒ.አ በፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ስም ከጨረታ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡ ከጨረታው መክፈቻ ዕለትና ሰዓት ዘግይቶ የቀረበ የጨረታ ሰነድ ውድቅ ይደረጋል፤ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በጨረታ ሰነዱ ክፍል 1 ላይ በተገለፀበት ቀንና ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ቤቶቹን በአካል ጨረታው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ እስከ ማብቂያው ቀን ድረስ በሥራ ቀናት ከጠዋቱ 3:00 እስከ ቀኑ 11፡00 ሰዓት ቤቶቹ በሚገኙበት አድራሻ ድረስ በመቅረብና ለዚሁ ሥራ በሚመደቡ ባለሙያዎች እና በሚወጣው ፕሮግራም መሰረት ቤቶቹን መመልከት ይችላሉ፡፡
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011-8-55-36-12/ 011-8-55-36-17/
09-11-80-92-63 ወይም 09-13-35-62-32 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
ዌይሳይት website:- www.fhc.gov.et
የፖ.ሣ.ቁ. P.O. Box 299
ፋክስ ቁጥር: 011-5-54-60-45/ 011-5-52-46-46
የፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን
