የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት አገልግሎት የሚውሉ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ ኮምፒዩተር፣ ቪዲዮ ካሜራ እና ፎቶ ካሜራ አክሰሰሪዎች፣ FM Radio Transmission እና ሶላር ጄኔሬተር /solar battery and panel/ እና የቢሮ መኪና ጎማዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎችን ማለትም፡-
ሎት 01 የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ኮምፒዩተር ቪዲዮ ካሜራ እና ፎቶ ካሜራ አክሰሰሪዎች፣
ሎት 02 FM Radio Transmission እና ሶላር ጄኔሬተር /solar battery and panel/፣
ሎት 03 የቢሮ መኪና ጎማዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾችን ይጋብዛል።
- ከላይ የተጠቀሰውን ዕቃ ቀጥታ ግንኙነትና አግባብነት ያላቸውና የዘመኑን ወይም የ2017 ዓ.ም የንግድ ፈቃድ ያሳደሱ፣ እንዲሁም በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባቸው የምስክር ወረቀት እና የቫት /የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያሳይ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩባቸው ሎት 01፣ ሎት 02 እና ሎት 03 የጨረታ ማስከበሪያ ብር 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማወዳደሪያ ሰነድ የማይመለስ ብር 150 /አንድ መቶ ሃምሳ ብር/ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግሥት የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት ገንዘቡን በመከፈል ደረሰኙን በመያዝ የጨረታ ሰነዱን በቢሮያችን G+2 ሕንፃ ግዥ ፋይናንስ ንብረት አስ/ር ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን የቴክኒካልና የፋይናንሻል ሰነድ በመለየት በታሸገ ፖስታ በማድረግ ኦሪጅናል እና ኮፒ በመለየት ፊርማና የድርጅቱን ማህተም በማሳረፍ የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት የግዥ ፋይናንስ ንብረት አስ/ር ሥራ ሂደት ቢሮ ለዚህ ጨረታ አገልግሎት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ይህ ማስታወቂያ በግልጽ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15/ አስራ አምስት/ ተከታታይ የሥራ ቀናት አየር ላይ ይቆያል ፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ላይ ታሽጎ ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- 16ኛው ቀን የመንግሥት የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የመንግሥት የሥራ ቀናት ጨረታው በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ ይከፈታል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ የሆነው አቅራቢ ዕቃዎችን አጓጉዞ በደቡብ ምዕራብ ኢ/ያ/ሕ/ክ/መ/ ሸካ ዞን በማሻ ከተማ የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት ማቅረብ አለበት፡፡
- ውል እንዲገባ ከተጻፈበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው ቀን ድረስ ዕቃዎችን በራሱ አጓጉዞ ማዘጋጀት /ማቅረብ/ አለበት፡፡
- ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ ከጠቅላላ ዋጋ 10% ለማስያዝ ፈቃደኛ መሆን አለባቸው፡፡
- የሚቀርቡ እቃዎች ጥራት ያላቸውና በተሰጣቸው እስፔስፊከሽን መሰረት አሟልተው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ማሳሰቢያ፡- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፍል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ፡-047-558-0788፣ 047-558-0965 ደውለው መጠየቅ ይቻላል።
የሸካ ማህበረሰብ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት
