ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በዋናው መ/ቤት ፋብሪካ ቅጥር ግቢ ያገለገሉ አሮጌ እና ዳግም አገልግሎት መስጠት የሚችሉ የተለያዩ መጠን ያላቸው የብረት ፓኔሎች፣ የውሃ ፓምፕ፣ የግንባታ ቫይብሬተር ከአክሰሰሪ ጋር ባሉበት ሁኔታ በጅምላ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡-01/2018
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በዋናው መ/ቤት ፋብሪካ ቅጥር ግቢ ያገለገሉ አሮጌ እና ዳግም አገልግሎት መስጠት የሚችሉ የተለያዩ መጠን ያላቸው የብረት ፓኔሎች፣ የውሃ ፓምፕ፣ የግንባታ ቫይብሬተር ከአክሰሰሪ ጋር ባሉበት ሁኔታ በጅምላ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ማንኛውም ተጫራች ንብረቶቹ ባሉበት መካኒሳ ዋናው መስሪያ ቤት በመመልከት እና የጨረታ ሰነዱን በብር 100 /አንድ መቶ ብቻ/ 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 309 በመግዛት ከጥቅምት 10 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 25 /2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ለጠቅላላው ንብረቶች የጅምላ ዋጋ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በመክተት መጫረት የሚቻል መሆኑን እየገለጽን ማንኛውም ተጫራች በቅድሚያ የጨረታ ማስከበሪያ ብር በባንክ በተረጋገጠ በሲፒኦ 30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) በኤንቨሎፕ በታሸገ ፖስታ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማስገባት ይኖርበታል፡፡ ጨረታው ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ተጫራቾች /ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት መካኒሳ ዋናው መስሪያ ቤት ይከፈታል፡፡
ድርጅቱ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር፡- 09114602479 ወይም 0911148521 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
