ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን እየገነባቸው ላሉት የ አዊ ዞን ከ/ፍ/ቤት፣ ፈ/ህይወት ሆስፒታል፣ ዋንዛየ ሎጂ እና ጎንደር ቄራ ግንባታ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የሚውሉ የውሃ ስርገት መከላከያ አቅርቦት እና ገጠማ ስራ እና የተለያዩ የሳኒተሪ እቃዎች አቅርቦት ግዥ ለመፈጸም ህጋዊና ብቃት ያላቸው ፋብሪካዎችና አቅራቢዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር 13/2018
ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን እየገነባቸው ላሉት የ አዊ ዞን ከ/ፍ/ቤት፣ ፈ/ህይወት ሆስፒታል፣ ዋንዛየ ሎጂ እና ጎንደር ቄራ ግንባታ ፕሮጀክቶች አገልግሎት የሚውሉ የውሃ ስርገት መከላከያ አቅርቦት እና ገጠማ ስራ እና የተለያዩ የሳኒተሪ እቃዎች አቅርቦት ግዥ ለመፈጸም ህጋዊና ብቃት ያላቸው ፋብሪካዎችና አቅራቢዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን እየገለጽን፤
- በዘርፉ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድና፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያለው/ያላት፤ ጨረታ ለመሳተፍ የታክስ ክሊራንስ ያለው/ያላት፤
- የጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ቫትን ጨምሮ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ዋስትና ማስያዝ ይኖርበታል፣
- የጨረታ ሰነዱን ባ/ዳር ከተማ ዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ቀበሌ 11 እና አ/አበባ ለገሃር አመልድ ህንፃ በሚገኘው ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ቢሮ 7ኛ ፎቅ ለተጠቀሱት ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት እንዲሁም ለሊፍት እና ጀነሬተር 20 ተከታታይ ቀናት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀናት ተጫራቾች የዕቃ አቅርቦቶችን እና የውሀ ስርገት አቅርቦትና ገጠማ የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናልና ኮፒውን በመለየት በተለያዩ ፖስታዎች በጥንቃቄ በማሸግ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን (15 ተከታታይ ቀናትን በመቁጠር) እንዲሁም ለጀነሬተር እና ሊፍት አቅርቦት እና ገጠማ እስከ 20ኛው ቀን (20 ተከታታይ ቀናትን በመቁጠር) ቴክኒካልና ፋይናንሻል ኦጅናልና ኮፒ በመለየት ባህር ዳር ዋናው ቢሮ 1ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 108 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል። ከላይ በተጠቀሱት ቀናት 8፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል። የተጠቀሱት የመክፈቻ እና የመዝጊያ ቀናቶች የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን እስከ ቀኑ 8፡00 ሠዓት ድረስ ማስገባት የሚችሉ ሲሆን በእለቱ ቀን 8፡00 ሰዓት ሳጥኑ ታሽጎ 8፡30 ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ለማንኛውም ተጨማሪ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር
ባህር ዳር 058-218-0538/09-21-25-89-20/
አዲስ አበባ ፡- ስልክ ቁጥር 0111265338/0930352410/0967994210
የዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
