በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖረሽን ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በሲሚንቶ ምርት ግብዓት የሚጠቀምበት ፑሚስ ብዛቱ 50,000 ቶን የሆነ ሙገር እና ታጠቅ ለማቅረብ የሚችሉትን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ::
የሀገር ውስጥ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ሙሲፋ/04/ 2018
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖረሽን ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ በሲሚንቶ ምርት ግብዓት የሚጠቀምበት ፑሚስ ብዛቱ 50,000 ቶን የሆነ ሙገር እና ታጠቅ ለማቅረብ የሚችሉትን በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል :: ስለዚህ ሕጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣የዘመኑን ግብር የከፈሉና የተጨማሪ እሴት ታከስ እና ታከስ ከፋይ ተመዝጋቢ የሆኑ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ኮፒ በመያዝ ተጫራቾች የማይመለስ 575.00 (አምስት መቶ ሰባ አምስት ብር) ከተጨማሪ እሴት ታከስ ጋር በመከፈል የጨረታ ሰነዱን አዲስ አበባ በቅሎ ቤት አካባቢ ጋራድ ህንፃ ቢሮ ቁጥር 432-3-8 ከሚገኘው የግዥ መምሪያ ቢሮ እየቀረቡ መግዛት ይችላሉ፡፡ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ብር 500,000.00 ( አምስት መቶ ሺህ ብር ) በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ሙገር ሲሚንቶ 4 (Chemical Industry Corporation Mugher Cement Factory) ስም በባንክ በተረጋገጠ ቼክ (C.P.O) ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ ባንከ ጋራንቲ ከቴክኒክዶከመንቶቹ ጋር በማያያዝ ይህ ጨረታ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም.ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ድረስ በሰም በታሸገ ኤንቨሎኘ የጨረታ ሰነዳቸውን አዲስ አበባ በሚገኘው በግዥ መምሪያ ቢሮ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዕለቱ ህዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም.ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት በግዥ መምሪያ ቢሮ ይከፈታል፡፡ ፋብሪካው ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር 0114420216
ፋክስ 0114420688
አዲስ አበባ
በኬሚካል ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን
ሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ
