የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ የሩዝ መፈልፈያ ማሽን እና የፖለቲውን ቲውብ ግዥ በሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የቤ/ጉ/ክ/መ/ግብርና ቢሮ
- የሩዝ መፈልፈያ ማሽን ግዥ ጨረታ ቁጥር 08/2018 ዓ/ም
- የፖለቲውን ቲውብ ግዥ ጨረታ ቁጥር 09/2018 ዓ/ም
ከላይ የተገለፁትን ግዥ ለመፈፀም የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለ2017/18ዓ/ም በዘርፉ የታደሠ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ፤ ለ2017/18 ዓ/ም የታደሰ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት በሀገር ውስጥ ገቢዎች የጨረታ ተሳታፊነት የድጋፍ ደብዳቤ ያለውን የታደሠ የአቅራቢነት ሰርትፊኬት ያላቸውን ተወዳዳሪዎች በሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- ዝርዝር ጨረታውን የያዘ ሠነድ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል አሶሳ በቤ/ጉ/ክ/መ/ግብርና ቢሮ በግዥ/ብ/አስ/ዳይሬክቶሬት በመቅረብ መግዛት ይቻላሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- አሸናፊ ድርጅት የውል ስምምነት ሲፈርም ለውል ማስከበሪያ ካሸነፈበት ጠቅላላ ዋጋ 10% ያስይዛል።
- በጨረታው ያልተመረጡ ተጫራቾች ያስያዙት የጨረታ ማስከበረያ የጨረታ አሸናፊ እንደታወቀ ወዲያውኑ ተመላሽ ይደረግላቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 15 ቀናት የጨረታ ሠነዱን በመግዛት እስከ 16ተኛው ቀን ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው የሚዘጋበት ቀን በ16ኛው የስራ ቀን ከጥዋቱ 4፡00 ሰዓት ሆኖ ነገር ግን ቅዳሜ እሁድ እና የህዝብ በዓል ቀን ላይ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይዘጋል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በ16ኛው የስራ ቀን ከጥዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አሶሳ በሚገኘው በቤ/ጉ/ክ/መ/ግብርና ቢሮ በግዥ ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት ይሆናል፡፡
- ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- 0577752144 አሶሳ ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ግብርና ቢሮ
