በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ሀረርጌ ቅ/ጽ/ቤት ጋራ ሙለታ ዲስትሪክት እና ወለጋ ቅ/ጽ/ቤት ቄለም ወለጋ ዲስትሪክት ላይ የቁም የፈረንጅ ጥድ ግንዲላ እንዲሁም ኢሉ አባ ቦራ ቅ/ጽ/ቤት ያዮ እና ሲቦ ቶሊ ቆቦ ዲስትሪክት ላይ የቁም የፈረንጅ ጥድ እና የ “Grevillea robusta” ግንዲላ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ
የቁም ደን ሽያጭ ጨረታ
ማስታወቂያ ቁጥር OFWEGU 07/2018
በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ሀረርጌ ቅ/ጽ/ቤት ጋራ ሙለታ ዲስትሪክት እና ወለጋ ቅ/ጽ/ቤት ቄለም ወለጋ ዲስትሪክት ላይ የቁም የፈረንጅ ጥድ ግንዲላ እንዲሁም ኢሉ አባ ቦራ ቅ/ጽ/ቤት ያዮ እና ሲቦ ቶሊ ቆቦ ዲስትሪክት ላይ የቁም የፈረንጅ ጥድ እና የ “Grevillea robusta” ግንዲላ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም
- የግንዲላ እና የእንጨት መሰንጠቂያ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፤ የቫት (VAT) ተመዝጋቢና /TIN number/ ያላቸው ድርጅቶች እና ግለሰቦች እንዲሁም ስለጨረታው ዝርዝር ሁኔታ የሚገልጽ የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዳቸው የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ቀበና ሼል/ ኦይል ሊቢያ አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ዋና መ/ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201 እና ጨረታው በወጣበት ኢሉ አባ ቦራ ቅ/ጽ/ቤት መቱ ከተማ፤ ወለጋ ቅ/ጽ/ቤት ጊምቢ ከተማ እና ሀረርጌ ቅ/ጽ/ቤት ጭሮ ከተማ በመግዛት በጨረታው መሣተፍ ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ይቆይል፡፡
- ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ትክክለኛው ቀንና ሰዓት በጨረታዉ ሰነድ ውስጥ ይገለጻል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid bond) የሚሆን ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 5% በማስላት በድርጅቱ ዋና መ/ቤት የምትጫረቱ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከሚገኙ ባንኮች በቅ/ጽ/ቤት የምትጫረቱ መ/ቤቱ ከሚገኝበት ከተማ በባንክ በተረጋገጠ ደረሰኝ (CPO) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0111240249 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት
