የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ ቀጥሎ የተጠቀሱትን የቁም ደኖች (የባህር ዛፍ ግንድ፣ ማገዶ፣ ፖል እና አጠናን) ለተለያዩ ኮንስትራከሽን ስራ የሚውል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የቁም ባህርዛፍ ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር B001/OFWEBB/2018
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ ቀጥሎ የተጠቀሱትን የቁም ደኖች (የባህር ዛፍ ግንድ፣ ማገዶ፣ ፖል እና አጠናን) ለተለያዩ ኮንስትራከሽን ስራ የሚውል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ለመጀመርያ ጊዜ የወጣ
- በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ አሎሼ ባቱ ዲስትሪከት
- በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ ጎሮ በሌ ዲስትሪክት
- በኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ ኩባዩ ዲስትሪክት
- በአሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ መና አንጌቱ ዲስትሪክት
በመሆኑም
- የግንዲላ፣ የአጣና፣ የእንጨት መሰንጠቂያ እና ተዛማጅ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው ድርጅቶችና ግለሰቦች እንዲሁም የዘመኑን ግብር የከፈሉና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ ስለ ጨረታዉ ዝርዝር ሁኔታ የሚገልጽ የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዳቸው 200 /ሁለት መቶ ብር/ የማይመለስ በመክፈል ባሌ ጎባ መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ሜድስን ፋካልቲ ፊት ለፊት በሚገኘው የኦሮምያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 2 በመግዛት በጫረታው ላይ መሳተፍ ይችላሉ፡፡
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ለ 15 ተከታታይ ቀናት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት እና የሚዘጋበት ትክክለኛው ቀንና ሰዓት በጨረታው ሰነድ ውስጥ ይገለፃል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚሆን ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ 5% በማስላት በባንከ በተረጋገጠ ደረሰኝ (CPO) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ወረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ ፡ በስልክ ቁጥር 0226611679 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የኦሮሚያ ደንና ዱር እንስሳት ድርጅት ባሌ ቅርንጫፍ
