ቦሌ ማተሚያ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ባንከ 45 ግራም 82 ወይም 84 ሴ.ሜ ነጭ ጥቅል ወረቀት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የሀገር ውስጥ ግዢ ጨረታ ማስታወቂያ
ቦሌ ማተሚያ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ባንክ 45 ግራም 82 ወይም 84 ሴ.ሜ ነጭ ጥቅል ወረቀት በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
1. ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፍቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የቫት ተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት፣ የንግድ ሰርተፍኬት እና ሌሎችም የህጋዊነት ማረጋገጫ ሰነዶች ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
2. ተጫራቾች በቅድሚያ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ/ ቢሮ ቁጥር 101 በመክፈል ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15/አስራ አምስት ተከታታይ ቀናት ድረስ ቦሌ መንገድ ከከቶታል ነዳጅ ማደያ ዝቅ ብሎ በሚገኘው ቢሯችን መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የዋጋውን 2% በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲፒኦ በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች ቴከኒካል እና ፋይናንሺል ሰነዶችን በአንድ ፖስታ አሽገው ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከግዥ ከፍል በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ያስገባሉ፡፡
5. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው 15ኛው ቀን ከረፋዱ 3፡00 ሰዓት ላይየጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ በዚሁ እለት በ3፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማህበሩ የስብሰባ አዳራሽ የግዢ ከፍል ይከፈታል፡፡ 15ኛው ቀን በዝግ ቀን ከዋለ በቀጣይ የሥራ ቀን ይከፈታል፡፡
6, ድርጅቱ ሌላ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ፦
ቦሌ መንገድ ከቶታል ነዳጅ ማደያ ዝቅ ብሎ
ስልክ ቁጥር፡-01115 15 50 05/0115 51 88 72
ፋክስ:-011551 86 96
ፖ.ሳ.ቁጥር 2365
አዲስ አበባ
ቦሌ ማተሚያ ኃ.የተ.የግ.ማህበር
