በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ጽ/ቤት ሊያስገነባው የፈለገውን የተለያዩ የግንባታ ሥራዎች ለመሰረት ዲዛይን (foundation design) ለማዘጋጀት ግንባታው የሚያርፍበትን በተመረጡ ቦታ ላይ እስከ 3 ሜትር ጥልቀት ቆፍሮ የአፈር ናሙና በመውሰድ አጠቃላይ የአፈር ናሙና ምርመራ ውጤት (soil investigation report and foundation recommendation) ሠርቶ
የምክር አገልግሎት የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር አ/ማ 002/2018 ዓ.ም
በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ጽ/ቤት ሊያስገነባው የፈለገውን የተለያዩ የግንባታ ሥራዎች ለመሰረት ዲዛይን (foundation design) ለማዘጋጀት ግንባታው የሚያርፍበትን በተመረጡ ቦታ ላይ እስከ 3 ሜትር ጥልቀት ቆፍሮ የአፈር ናሙና በመውሰድ አጠቃላይ የአፈር ናሙና ምርመራ ውጤት (soil investigation report and foundation recommendation) ሠርቶ የሚያስረክብ በዘርፉ የተመዘገበ ደረጃ 5 እና ከዚያ በላይ የሆኑ አማካሪ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል። በመሆኑም ለሥራው አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን፣ የሰው ኃይል በማቅረብ የሚሠሩ ድርጅቶች ከዚህ በታች በተጠቀሰው መስፈርት በማሟላት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
|
ሎት |
የሥራው አይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና |
ደረጃ |
የጨረታ ሰነዱ መሸጥ የሚጀመርበት ቀን |
የጨረታ ማስገቢያ ቀን |
የጨረታ መክፈቻ ቀን |
|
ሎት-1 |
የወረዳ 07 ቀበና ጤና ጣቢያ G+5 ሕንፃ ግንባታ |
20,000 ብር |
ደረጃ-5 እና ከዚያ በላይ |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት 2፡30 – 10፡00 ሰዓት |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 – 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው የሥራ ቀን ከ4፡14 ሰዓት ጀምሮ |
|
ሎት-2 |
የወረዳ 07 ፖሊስ መምሪያ G+4 ሕንፃ ግንባታ |
20,000 ብር |
ደረጃ-5 እና ከዚያ በላይ |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት 2፡30 – 10፡00 ሰዓት |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 – 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው የሥራ ቀን ከ4፡14 ሰዓት ጀምሮ |
|
ሎት-3 |
ገነት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት ጂ+4 ግንባታ መመገቢያ እና ማስፋፊያ |
20,000 ብር |
ደረጃ-5 እና ከዚያ በላይ |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት 2፡30 – 10፡00 ሰዓት |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 – 4፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ |
በጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው የሥራ ቀን ከ4፡14 ሰዓት ጀምሮ |
አማካሪዎች ድርጅቶች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች፡-
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ ለመውሰድ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ህጋዊ ዶክሜንታችሁን ዋናውንና አንድ ኮፒ ማቅረብ ይጠበቅባችኋል።
1. በዘርፉ የ 2017/2018 ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፤ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና የምዝገባ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉና በጨረታ መሳተፍ የሚያስችል ታክስ ክሊራንስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
2. ከመንግሥት ግዥና ንብረት ማስወገድ ኤጀንሲ የተመዘገቡ ምስክር ወረቀት ያላቸው፤
3. ማንኛውሞ ሥራ ተቋራጭ ሆነ አማካሪ ከፈዴራል ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የምስክር ወረቀት ያላቸው እና ከአዲስ አበባ ከተማ ግንባታ እና ፍቃድ ቁጥጥር ባለሥልጣን ተመዝግቦ የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ሳይዝ በጨረታው መሳተፍ አይችልም፡፡
4. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በአየር ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከላይ የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ዋናውን (orginal) እና የማይመለስ ቅጂ (copy) ይዞ በመቅረብ የማይመለስ 1000.00 (አንድ ሺ ብር) በመክፈል በአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ጽ/ቤት የምህንድስና ግዥ ቡድን 5ኛ ፎቅ በሚገኘው ቢሮ ቀርበው ዘወትር በሥራ ሰዓት ከ2፡30 እስከ 10:00 ሰዓት ድረስ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
5. ጨረታው የሚከፈተው በ16ኛው የሥራ ቀን በእለቱ ባለቤቱና ተጫራቾች ወይንም ሕጋዊ ወኪሎች በተገኙበት በጽ/ቤቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ከረፋዱ 4:15 የሚከፈት ይሆናል፡፡
6. ማንኛውም ተጫራቾች ለ90 ቀናት የሚያገለግል የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና / BID BOND / በባንክ የክፍያ ትዕዛዝ (CPO) ወይም የባንክ ጋራንቲ (UnConditional Bank Guarantee) ከላይ በተጠቀሰው እና በሚሳተፉበት ፕሮጀክት የብር መጠን 20,000 (ሃያ ሺህ ብር) ማቅረብ ግዴታ አለበት፡፡ የቀረበው የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማቅረብ ያለበት በቴክኒካል ኦርጂናል ሰነድ ውስጥ ወይም ከፖስታ ውጪ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
7. ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነድ አንድ ኦሪጅናል እና ሁለት ኮፒ ፋይናንሽያል ሰነድ አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ በድምሩ ስድስት ሰነድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ በተጨማሪም የታሸገውን 6 ፖስታ በአንድ እናት ፖስታ የድርጅቱን ማህተም እና የሚወዳደሩበትን የሥራ አይነት ስም በመጻፍ ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡ የጨረታው ፋይናንሻል ሰነድ ላይ ያልተፈረመ ሆኖ ስርዝ ድልዝና በፍሉድ የተስተካከለ ዋጋ ከሆነ ሙሉ ለሙሉ ከጨረታው ያሰርዛል፡፡
8. ተጫራቾች የሥራዎችን የዋጋ ዝርዝር እና የጨረታ መወዳደሪያ ላይ ስማቸውን ፊርማቸውን፣ አድራሻቸውን ማስፈር ማህተም ማድረግ ኤንቨሎፑን በማሸግ ማስታውቂያው በወጣበት በ16ኛው የሥራ ቀን በአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ጽ/ቤት የምህንድስና ግዥ ቡድን 5ኛ ፎቅ በሚገኘው ቢሮ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ እስከ 4፡00 ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
9. ተጫራቾች ከዚህ በፊት በአራዳ ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ጽ/ቤት ምንም አይነት ውል ያላቋረጡ መሆን ይጠበቅባቸዋል።
10. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከማስገባታቸው በፊት የተጫራቾችን መመሪያ (Instructon to Bidder (ITB) and Scope of Consultancy service) እንዲያነቡ ይመከራል።
11. አማካሪ ድርጅቱ ሥራውን በጥራት ለማከናወን የሚከተላቸውን መሰረታዊ እስትራቴጂዎችን የሚያቀርብ፤ እነዚህም ባለመፈጸማቸው ተጠያቂ እንደሚያደርገው ማረጋገጫ የጻፈና በሥራ አስኪያጅ ወይም በኃላፊው የተፈረመ ሆኖ ማህተም ያለው ሰነድ የሚያቀርብ መሆን አለበት፡፡
12. አሠሪው መ/ቤት አሸናፊው ካሸነፈበት አጠቃላይ የሥራ መጠን 20% መጨመርም ሆነ መቀነስ ይቻላል።
13. ተጫራቾች የሚያቀርቡት የድርጅቱ የሥራ ልምድና ማንኛውም በቴክኒካል የተጠየቁት ዶክመንቶችን አሠሪው መ/ቤት ኦርጂናል ዶክመንት ከሰጠው አካል የማጣራት ሙበት የተጠበቀ ነው።
14. ጽ/ቤቱ ባወጣው የአማካሪ ጨረታዎች ከአንድ ፕሮጀክት በላይ መግዛት የሚቻል ሲሆን መጫረት የሚፈቀደው በአንድ በመረጡት ፕሮጀክት ብቻ ይሆናል፡፡
15. ጨረታውን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማስታወቂያው በወጣበት በ16 ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 4:15 ጀምሮ በአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳዳር ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ጽ/ቤት የምህንድስና ግዥ ቡድን 5ኛ ፎቅ በሚገኘው ቢሮ ይከፈታል። የጨረታው መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም በበዓል ቀን ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት እና ቦታ የሚከፈት ይሆናል።
16. ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ አራት ኪሎ በሚገኘው በአራዳ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ጽ/ቤት የምህንድስና ግዥ ቡድን 5ኛ ፎቅ በሚገኘው ቢሮ በአካል በመቅረብ መረዳት ይችላሉ፡፡
የአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር ዲዛይንና ግንባታ ሥራዎች ጽ/ቤት
