የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ የሲ.ሲ.ቲ.ቪ ካሜራዎች በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የሀገር ውስጥ ግልፅ ጨረታ ቁጥር 24/2018
- የሲ.ሲ.ቲ.ቪ ካሜራዎች አቅርቦት ግዥ
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የሚከተሉትን ህጋዊ ሰነዶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡-
- የታደሰ ንግድ ፍቃድ
- ቫት ተመዝጋቢ
- ታክስ ክሊራንስ
- በግዥ ባለስልጣን የምዝገባ ማስረጃ
- የታክስ ከፋይነት ምዝገባ ሠርተፍኬት
- በዘርፉ የአቅራቢነት ምዝገባ ሠርተፍኬት ወረቀት
- ጨረታው ፀንቶ የሚቆየው ለ 30 (ሰላሳ) ቀናት
- የጨረታ ማስከበሪያ መጠን 60,000.00 (ስልሳ ሺህ) ብር ሆኖ የጨረታ ማስከበሪያው በሲ.ፒ.ኦ የባንክ ዋስትና መሆን ይኖርበታል
- ሰነድ ለመግዛት የምትፈልጉ ተጫራቾች ሰነዱ በሚገኝበት በኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ ዋና መስሪያ ቤት በግዥ ክፍል ቢሮ. ቁጥር 01 የማይመለስ 300.00 (ሶስት መቶ) ብር በመክፈል መውሰድ ትችላላችሁ።
- የጨረታ ማስረከቢያ የመጨረሻ ቀን እና ሰዓት 06/04/2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 9፡00 ሰዓት
- ጨረታው የሚከፈተው፡- በዕለቱ 06/04/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9፡30 ሰዓት
- ኢንተርፕራይዙ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
- ለበለጠ መረጃ እና ማብራሪያ ዋናው መስሪያ ቤት በአካል በመገኘት ወይም በስልክ 0114171703 መጠየቅ ይቻላል።
አድራሻ፡-
- የኢትዮጵያ የክፍያ መንገዶች ኢንተርፕራይዝ (ዋና መስሪያ ቤት ቱሉ ዲምቱ)
