የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ ለዳውሮ ዞን ዛባጋዞ ወረዳ እና ለምዕራብ ኦሞ ዞን ሱሪ ወረዳ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ምገባ አገልግሎት የሚውል ያልተፈጨ በቆሎ ፣ የውጭ ሩዝ ፣ ቦሎቄ ፣ የምግብ ዘይት እና ጨው በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር - ት/ቢ/ግ/ጨ/- 02/18
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ትምህርት ቢሮ ለዳውሮ ዞን ዛባጋዞ ወረዳ እና ለምዕራብ ኦሞ ዞን ሱሪ ወረዳ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ምገባ አገልግሎት የሚውል ያልተፈጨ በቆሎ ፣ የውጭ ሩዝ ፣ ቦሎቄ ፣ የምግብ ዘይት እና ጨው በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ አቅራቢዎች እንዲወዳደሩ ይጋበዛል።
- በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያላቸው
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ
- በአቅራቢነት የተመዘገቡ
- ከዘመኑ ግብርና ታክስ ነጻ የሆኑ
- የሚቀርቡት እህሎች የግብርና ምርቶች ጥራት ያላቸውና የፋብሪካ ውጤቶች የጥራት ደረጃቸው የተረጋገጡ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ከክልሉ ትምህርት ቢሮ ታርጫ ከተማ ግ/ፋ/ን አስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ የማይመለስ ብር 400 /አራት መቶ ብር/ በኢን.ባ በቢሮው ሂሳብ ቁጥር 1000453714528 በማስገባት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ጨረታው ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት እስከ ቀኑ 11፡30 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከታወቀ ባንክ C.P.O. ፣ በካሽ ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ብር 50,000 /ሃምሳ ሺህ ብር/ ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ህጋዊ የንግድ ማስረጃ ፣ CPO እና ቴክኒካል ሰነድ ዋናና ኮፒ ለየብቻ በሁለት ፖስታ፣ የዋጋ ፖስታ ዋናና ኮፒ ለየብቻ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተከታታይ ቀናት በ16ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ ይዘጋል። እንዲሁም በዚሁ ዕለት ከቀኑ 8፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በክልሉ ትምህርት ቢሮ ግ/ፋ/ን/አስ/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ይከፈታል።
- በመክፈቻው ዕለት ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው ባይገኙም ጨረታው ይከፈታል። ቢሮው ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልግዎ:- በስልክ ቁጥር 0473450715 መጠየቅ ይችላሉ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግሥት ትምህርት ቢሮ
