የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት መንገዶች ባለሥልጣን ዋና መ/ቤት በተለያዩ ፕሮጀክቶችና ጥገና ጽ/ቤቶች ለሚያከናውናቸው የመንገድ ግንባታ እና ጥገና ሥራ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ማሽነሪዎችን ማለትም ዶዘር፣ ኤክስካቫተር እና ሮለር በጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል፡፡
ለሶስተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
003/2018
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት መንገዶች ባለሥልጣን ዋና መ/ቤት በተለያዩ ፕሮጀክቶችና ጥገና ጽ/ቤቶች ለሚያከናውናቸው የመንገድ ግንባታ እና ጥገና ሥራ አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ማሽነሪዎችን ማለትም ዶዘር፣ ኤክስካቫተር እና ሮለር በጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ዝርዝር መሰረት አቅራቢዎችን ይጋብዛል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችላቸውን የዘመኑን ግብር የተከፈሉበትን ከሚፈለገው አገልግሎት ጋርየተዛማጅ የንግድ ሥራ ፍቃድ ወይም የአገልግሎት ሥራ ፍቃድ፣ የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር እና በጨረታው ለመሳተፍ ከሀገር ውስጥ ገቢ ቢሮ የድጋፍ ደብዳቤ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ዋጋቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ የፋይናንሻል እና ቴክንካል ፕሮፖዛሉን በተለያየ ፖስታ በማድረግ አንድ ዋና እና ሁለት ኮፒ አርጅናል›› እና «ኮፒ» በማለት እና የጨረታ ማስከበሪያውንም ለእያንዳንዱ ማሽን በተለያየ ፖስታ ለየብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ) ብር በባለሥልጣን መ/ቤቱ የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000642058936 ገቢ በማድረግና የባንክ ደረሰኝ ይዞ በመቅረብ ከባለሥልጣን መ/ቤቱ ግዥ እና ንብረት እስተዳደር ኬዝ ቲም ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- የጨረታ አሸናፊ የሚወሰነው በጨረታ ሰነዱ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሰረት ሲሆን ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም አቅራቢ ክፍት ነው፡፡
- አቅራቢዎች ጨረታውን ለዚህ ተግባር ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ገቢ የሚያደርጉት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛ ቀን ሲሆን ጨረታው እስከ ቀኑ 11፡30 ሰዓት ድረስ ይሆናል፡፡ ጨረታው 16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ቀን 3፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል።
- ተጫራቾች የጠቅላላ ዋጋውን 1% የጨረታ ማስከበሪያ በቅድም ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም ሲፒኦ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ከዚህ ውጪ በኢንሹራንስ ወይም በሌላ መልክ የሚቀርብ የጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ደንብና መመሪያ መሰረት ጨረታቸውን ማቅረብ አለባቸው ከጨረታ ደንብ እና መመሪያ ውጪ የሚቀርብ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ተጫራቾች ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ በተመሳሳይ ዘርፍ ከሠሩበት የመንግሥት መ/ቤት ቢያንስ አንድ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ደብዳቤ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡
በምዕራብ ኦሞ ዞን ጀሞ ከተማ በሚገኘው የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል መንግሥት መንገዶች ባለሥልጣን ዋና መ/ቤት በግብዓት አቅርቦትና አስተዳደር ዘርፍ ግዥና ንብረት አስተዳደር ኬዝ ቲም ቢሮ በአካል በመቅረብ ማነጋገር ወይም በስልክ ቁጥር 0474527941/0474527727 ደውለው ማነጋገር ይችላሉ።
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልላዊ መንግሥት መንገዶች ባለስልጣን
