የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ በራስ ሀይሉ ስፖርት ትምህርት እና ስልጠና ማዕከል በግቢው ውስጥ የሚገኘውን ባለ18 ፓትራ የዳቦ ቤት መጋገሪያ ማሽን ከነሙሉ ዕቃው እና ከነመጋገሪያው ቦታ እንዲሁም ከነመሸጫው ቦታ ብቃት እና ፍቃድ ያላቸውን አካላት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ በራስ ሀይሉ ስፖርት ትምህርት እና ስልጠና ማዕከል በግቢው ውስጥ የሚገኘውን ባለ18 ፓትራ የዳቦ ቤት መጋገሪያ ማሽን ከነሙሉ ዕቃው እና ከነመጋገሪያው ቦታ እንዲሁም ከነመሸጫው ቦታ ብቃት እና ፍቃድ ያላቸውን አካላት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማከራየት ይፈልጋል። በመሆኑም ከታች በዝርዝር የተገለጹትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች በመወዳደር መከራየት ይችላሉ፡-
- ተጫራቾች የዘመኑን በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- የመስሪያ ካፒታል 800,000 /ስምንት መቶ ሺህ ብር/ እና በላይ የባንከ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ከ2 ያላነሰ የመልካም ስራ አፈጻጸም የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከታች በተገለጸው መጠን መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ስም በተሰራ ሲ.ፒ.ኦ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
|
ተ.ቁ |
የአገልግሎት አይነት |
የግዥው ምድብ |
የግዝው ሎት ምድብ |
የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር |
የመክፈቻ ቀን ና ሰዓት |
|
1 |
የዳቦ ቤት ኪራይ አገልግሎት ከነሙሉ መጋገሪያ ማሽን ከነመሸጫ ቦታ እና መጋገሪያ ቦታ |
አገልግሎት |
ሎት 1 |
150,000 /አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር/ |
በ11ኛው ቀን 4፡30 |
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ለእያንዳንዳቸው በመክፈል ከቢሮአችን ከግዥ እና ንብረት አስተዳደር ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በአዲሱ ህንጻ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር ቢሮ ቁጥር 403 በመቅረብ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን አሟልቶ ፋይናንሺያል ዶክመንት ኦርጂናል እና ኮፒ በተለያየ ፖስታ እንዲሁም ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጂናል እና ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማሸግ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታተይ የስራ ቀናት በግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው አየር ላይ በዋለ በ11ኛው የስራ ቀን በ4፡00 የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ በዚያው እለት ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመስሪያ ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
- የጨረታ አሸናፊው እንደታወቀ ለጨረታ ማስከበሪያ የተያዘው ገንዘብ ለአሸናፊዎች ከ7 ቀን በኋላ ይመለሳል።
- የጨረታ አሸናፊው በተጫራቾች መመሪያ በተጠቀሰው መሰረት የጨረታ አሸናፊነቱ በጽሁፍ በተገለጸ በ7 /ሰባት/ ቀናት በኋላ አስፈላጊውን የውል ማስከበሪያ ገንዘብ በመያዝ ወዲያውኑ ወደ ስራ ክፍሉ መጥቶ ውል መፈረም አለበት፤ ይህ ባይፈጸም የጨረታ አሸናፊነቱን በመሰረዝ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ሲ.ፒ.ኦ ለመንግስት ገቢ ይደረጋል።
- ቢሮው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ማስታወሻ
- የመጋገሪያ ማሽኑ በሙሉ በመስሪያ ቤቱ የሚሟሉ ይሆናል /ከጄኔሬተር ውጪ።
- የውሃ እና መብራት አገልግሎት በነፃ ይሆናል።
- ተጫራቾች ሙሉ መረጃውን የጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጋገሪያ ማሽኑን እና የመጋገሪያ ቦታውን ማዕከሉ ድረስ በመሄድ ማየት ይችላሉ።
ተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011 812 0778 አድራሻ፡ ምርጫ ቦርድ አጠገብ ያለው ባህል እና ቱሪዝም ህንፃ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ
