Tender Detail

Tender Details

  • Company በኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፈዴሬሽን ኃላ/የተ/ አሰላ ብቅል ፋብሪካ
  • Address አዲስ አበባ ከተማ ከጀርመን አደባባይ ወደ ሚካኤል አደባባይ በሚወስደው መንገድ ላይ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፈዴሬሽን ሕንፃ ስድስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 ወይም አሰላ- ቁሉምሳ : ኢትዮጵያ, Phone: 09-65-65-04-81
  • Website
  • Deadline11 Jan 2026, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price500.00
  • opening date2026-01-12 00:00:00
  • Categories Plastic Raw Materials And Products

የኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፈዴሬሽን ኃላ.የተ እሰላ ብቅል ፋብሪካ ጥራትና ደረጃውን የጠበቁ የተለያዩ የብቅል ምርት ማሸጊያ ከረጢት፣ ተረፈ-ምርት መቋጠሪያ ከረጢት፣ የተበጠረ ገብስ መቋጠሪያ ከረጢት እና የእንስሳት መኖ ማሸጊያ ከረጢት አቅም እና ፍላጎት ያላቸውን አምራች ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ በማወዳደር ለመግዛት ይፈልጋል፡፡


 

የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር: NCB/OACFLTD/AMF/14/2018

 

የኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፈዴሬሽን ኃላ.የተ እሰላ ብቅል ፋብሪካ ጥራትና ደረጃውን የጠበቁ የተለያዩ የብቅል ምርት ማሸጊያ ከረጢት፣ ተረፈ-ምርት መቋጠሪያ ከረጢት፣ የተበጠረ ገብስ መቋጠሪያ ከረጢት እና የእንስሳት መኖ ማሸጊያ ከረጢት አቅም እና ፍላጎት ያላቸውን ምራች ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ በማወዳደር ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው

  1. ተጫራቾች የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ዝርዝርውስጥ የተመዘገቡ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
  2. የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር ብቻ) በፋብሪካችን አካውንት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000257808697 ወይም በአሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ 1000043405229 በመክፈል/ገቢ በማድረግ)
  • ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ጠዋት 200-600 ከሰዓት በኋላ 700-1000 ሰዓት ድረስ ከጀርመን አደባባይ ወደ ሚካኤል አደባባይ በሚወስደው መንገድ ላይ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የአሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ሕንፃ ስድስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 ወይም አሰላ-ቁሉምሳ ከሚገኘው ፋብሪካችን ቢሮ ቁጥር 003 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  1. ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በፖስታ በማሸግ አዲስ አበባ በሚገኘው የፋብሪካችን ዋና /ቤት በኦሮሚያ ግብርና ኅብረት ሥራ ማኅበራት ፌዴሬሽን ኃላ.የተ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ከታች ከተጠቀሰው የመዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  2. ተጫራቾች ከመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ (CPO) ወይም Bank Guarantee ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. ተጫራቾች የፋይናንሽያል እና ቴክኒካል ፖስታቸውን በተለያየ ፖስታ በማሸግ በተቀመጠው ዝርዝር መስፈርት መስረት ሶስት ናሙና ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  4. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን፡-
  5. ጨረታው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 21 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን 22ኛው ቀን ከጠዋቱ 430 ሰዓት ተዘግቶ ከጠዋቱ 500 ሰዓት ላይ ለመገኘት በሚሹ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ በሚገኘው የፋብሪካችን ዋና /ቤት የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃላ/የተ 7 ፎቆ ላይ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ የመፈቻው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  6. ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  7. ተጫራቾች በጨረታ ማስታወቂያና በተጫራ መመሪያ ላይ ግልጽ ያልሆነ ነጥብ ካለና ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር፡- 09-65-65-04-81/09-65-65-02-85 በሥራ ሰዓት ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

 

የኦሮሚያ ግብርና ኀብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን .የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ

Save Tender