ኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክሲዮን ማህበር በአላት ሁለት ህንፃዎች በጨረታ አወዳድሮ ዙሪያውን ውጫዊ ገጽታ ብቻ ቀለም ማስቀባት ይፈልጋል፡፡
የህንፃ ቀለም ለማስቀባት የወጣ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክሲዮን ማህበር በአላት ሁለት ህንፃዎች በጨረታ አወዳድሮ ዙሪያውን ውጫዊ ገጽታ ብቻ ቀለም ማስቀባት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርበተቀመጠው የኮሪደር ልማት የህንፃ ቀለም ቅብ ደረጃ (Standard) መሰረት የውጭ ቀለም አክሲዮን ማህበሩ ቀለሙን አቅርቦ ሌሎች አስፈላጊ መሳሪያዎችንና የሕንጽ መወጣጫዎች በራሳቸው አሟልተው የሚሰሩ ተጫራቾችን የቀለም ቅብ በካሪ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ተጫሪቾች ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች-
- በዘርፋ 2018ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ እና የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት
- የቫት እና የግብር ከፋይነት ሰርተፍኬት (TIN Number)
- ለሚከፈለው ክፍያ ህጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ የሚችል፡
- ቢያንስ በተመሳሳይ ሥራ የሠራና ልምድ ማቅረብ የሚችል፡
- ማንኛውም ተጫራች ለጨረታ ለጨረታ ማስከበሪያ 20,000 ባንክ ሲፒኦ (CPO) አሰርቶ በማህበሩ ስም ማስያዝ የሚችል፡
- ከላይ የተጠቀሱትን ሁኔታዎች የሚያሟሉ የሥራ ተቋራጨች ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ 5 (በአምስት) የሥራ ቀናት የጨረታ ሰነድ ከአክሲዮን ማህበሩ የማይመለስ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) በመከፈል መግዛት የሚችሉ ሲሆን የማሉትን የመጫረቻ ዋጋቸውንና አሰፈላጊ ሰነዶችን በታሸገ ኢንቨሎፕ ማስገባት ትችላላችሁ።
- ጨረታው ከወጣበት ቀን አምስተኛው ቀን 8፡00 ሰአት ተዘግቶ በዛው ቀን 9፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአክሲዮን ማህበሩ ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ በማስተወቂያ ከተገለፀ በ2 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ አክሲዮ ማህበሩ ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ ውል መዋዋል ይጠበቅበታል። ይህ ካልሆነ ግን ስራውን በራሱ ፈቃድ እንደተወው ተቆጥሮ ያስያዘው የጨረታ ማስከበረያ ግንዘብ(CPO) ለማህበሩ ገቢ ይደረጋል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
-
- ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፈልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- አድራሻች፡- በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዮ ቦታው አጠና ተራ ከቴለው ጀርባ ባለው የአ/ማህበሩ የገበያ ማዕከል ሕንጽ ቁጥር 2 አራተኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 4
- ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥር 09-12-05-47-92 /09-32-08-03-77
የኮልፌ ቅዱስ ራጉኤል አዲስ ሕይወት አክሲዮን ማህበር
