Tender Detail

Tender Details

  • Company በአብክመ በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በዳዋ ጨፋ ወረዳ የሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት
  • Address በዳዋ ጨፋ ወረዳ የሸክላ ከተማ : አማራ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0910 24 55 51
  • Website
  • Deadline20 Jan 2026, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price400.00
  • opening date2026-01-20 00:00:00
  • Categories Land , House, Building And Warehouse

በአብክመ በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በዳዋ ጨፋ ወረዳ አስተዳደር የሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 ከ ሀ እስከ ሠ በተዘረዘረው መሰረት በሸክላ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ጠቅላላ ስፋቱ 4437 (አራት ሺ አራት መቶ ሰላሳ ሰባት) ካሬ ሜትር የሆነ ለንግድ እና ለመኖሪያ አገልግሎት የሚውሉ የልማት ቦታን በመደበኛ ጨረታ


አራተኛ ዙር የመሬት ሽያጭ የሊዝ ጨረታ ማስታወቂያ

 

በአብክመ በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በዳዋ ጨፋ ወረዳ አስተዳደር የሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ በሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 721/2004 አንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 እስከ በተዘረዘረው መሰረት በሸክላ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ጠቅላላ ስፋቱ 4437 (አራት አራት መቶ ሰላሳ ሰባት) ካሬ ሜትር የሆነ ለንግድ እና ለመኖሪያ አገልግሎት የሚውሉ የልማት ቦታን በመደበኛ ጨረታ አወዳድሮ በሊዝ ማስተላለፍ ይፈልጋል።

ስለሆነም በጨረታው ላይ ለመሳተፍ ፍቃድኛ የሆኑ ተጫራቾች -

1.     የጨረታውን ሰነድ በሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት በመሬት ልማትና ባንክ ቡድን ቢሮ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ሽያጭ የማይመለስ የኢትዮ ብር 400.00 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታውን ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡

2.     ተጫራቾች ቦታው የሚገኙበት ድረስ በመሄድ አጠቃላይ የቦታውን ሁኔታ በማየት ዋጋ ማቅረብ ይችላሉ።

3.     ተጫራቾች የሚያቀርቡት የጨረታ ሰነድ በተጫራቾች መመሪያ ሰነድ ላይ በቀረበው ስፔስፊኬሽን /Specification/ መሰረት መሆን ይኖርበታል።

4.     ተጫራቾች በሚወዳደሩበት ጠቅላላ ቦታ ስፋት በሊዝ መነሻ ዋጋ ተባዝቶ ከሚገኘው ውጤት 10 በመቶ ያላነሰ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ ክፍያ ማዘዣ /CPO/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል። ይህ ሳይሆን ቢቀር ወይንም 10 ከመቶ ቢያንስ ተጫራቹ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከውድድር ይሰረዛል።

5.     ተጫራች የጨረታውን ሰነድ፣ ሲፒኦ እና ሌሎች የጨረታ ሰነዶችን በታሸገ ኤንቨሎፕ በአብክመ በኦ//ዞን በሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት በመሬት ልማትና ባንክ ቡድን ቢሮ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን 28/4/2018 . እስከ 12/5/2018 . ከቀኑ 1100 ሰዓት ብቻ ማስገባት ይኖርባቸዋል።

6.     ጨረታው የሚዘጋበት ቀን 12/5/2018 . 1100 ሰዓት ይሆናል።

7.     ጨረታው የሚከፈትበት ቀን 13/5/2018 . 400 ሰዓት በሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት አዳራሽ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

8.     ቦታውን ለመጎብኘት ለሚፈልጉ ተጫራቾች ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 300 ሰዓት እስከ 1100 ሰዓት ለሽያጭ የተዘጋጁ ቦታዎች በሚገኙበት የሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት በሚመድባቸው አስጎብኝዎች ቦታዎቹን መመልከት ይችላሉ።

9.      የአካቢውን ወቅታዊ የሊዝ ጨረታ መነሻ ዋጋ እና ሌሎች የከተማ መሬትን በሊዝ ለማስተዳደር የወጣውን አዋጅ ቁጥር 721/2004 መሰረት በማድረግ የሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ መመልከት ይችላሉ።

10. የሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

 

ተጨማሪ መረጃ፡-

በስልክ ቁጥሮች 0910 24 55 51 /0923 66 11 18 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።

 

በአብክመ በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በዳዋ ጨፋ ወረዳ የሸክላ ከተማ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት

 

Save Tender