የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ለቀላልና ከባድ ተሽከርካሪዎች እና ማሽነሪዎች ከአገልግሎት የሚውል የተለያየ መጠን ያላቸው ባትሪዎች ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ማ/ኢ/መ/ባ/B5/18
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ለቀላልና ከባድ ተሽከርካሪዎች እና ማሽነሪዎች ከአገልግሎት የሚውል የተለያየ መጠን ያላቸው ባትሪዎች ብቁ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም
1. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችለውን የዘመኑን ግብር የተከፈለበትን ከሚፈለገው አገልግሎት ጋር የተዛመደ የንግድ ሥራ ወይም የአገልግሎት ሥራ ፈቃድ (የአቅራቢነት ምስክር ወረቀት፣ መንግስት መ/ቤቶች በሚያወጡት ጨረታ ላይ መሳተፍ የሚያስችል የምስክር ወረቀት የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡:
2. ተጫራቾች በታሸገ ኤንቨሎፕ የፋይናንሻል ዋና እና ሁለት ኮፒ የቴክኒካል ፕሮፖዛሉን ዋና እና ሁለት ኮፒ በተለያየ ፖስታ በማድረግ ኦሪጅናል እና ኮፒ በማለት እና የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በተለየ ፖስታ ለብቻው በማሸግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
3. ተጫራቾች ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 /ሦስት መቶ/ ብር ብቻ ለእያንዳንዱ ሎት በመክፈል ከባለስልጣኑ ዋና መ/ቤት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኬዝ ቲም ቢሮ መውሰድ ይችላሉ፡፡
4. የጨረታው አሽናፊ የሚወሰነው በጨረታ ሰነዱ ውስጥ በተመለከቱት መስፈረቶች መሰረት ሲሆን ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም አቅራቢ ክፍት ነው።
5. አቅራቢዎች ጨረታውን ለዚህ ተግባር በተዘጋጀ ሳጥን ገቢ የሚያደርጉበት ቀን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 22ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ድረስ ይሆናል። ጨረታው በዚያኑ ቀን ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባሉበት ይከፈታል፡፡ ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል፡፡
6. ተጫራቾች በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዘንድ ዕውቅና ካላቸው የፋይናንስ ተቋም በቅደመ ሁኔታዎቸ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም ሲ ፒ ኦ /c.p.o/ ለአንድ ባትሪ ዓይነትና መጠን ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ብቻ ፣ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። በኢንሹራንስ ዋስትና የሚቀርብ የጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡
7. ተጫራቾች በጨረታው ደንብና መመሪያ መሰረት ጨረታውን ማቅረብ አለባቸው። ከጨረታው ደንብና መመሪያ ውጭ የሚቀርብ ማንኛውም የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
8. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
9. ለበለጠ መረጃ የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን ግዥና ንብረት አስተዳደር ኬዝ ቲም፡፡
የስልክ ቁጥር 0113659932
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንገዶች ባለስልጣን
ወልቂጤ ኢትዮጵያ
