የምስራቅ ባሌ ዞን ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት ውስጥ ለሚገኙት የህግ ታራሚዎች በምግብ አቅርቦት የሚውል ጥሬ እህል ማጣፈጫና እና የማገዶ እንጨት ለ2018 ዓ.ም በጀት ለሁለተኛ ዙር ከየካቲት 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ/ም ለ 5 (አምስት) ወር በሚቆይ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የምስራቅ ባሌ ዞን ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት ውስጥ ለሚገኙት የህግ ታራሚዎች በምግብ አቅርቦት የሚውል ጥሬ እህል ማጣፈጫና እና የማገዶ እንጨት ለ2018 ዓ.ም በጀት ለሁለተኛ ዙር ከየካቲት 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ/ም ለ 5 (አምስት) ወር በሚቆይ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት ማንኛውም ጨረታ ውል መካፈል የሚፈልግ ድርጅት ወይም ግለሰብ፤
1. የገንዘብ እና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስቴር ወይም ቢሮ የዘመኑን የስራ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እና አግባብነት ያለው 2018 የታደሰ ንግድ ስራ ፍቃድ ያላቸው መሆን ይጠበቅባቸዋል፡፡
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) የተመዘገቡ ወይም የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ የሚያቀርቡ መሆን አለባቸው።
3. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 30 (ሰላሳ ብር) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት ከዞኑ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
4. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነዶቻቸውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ በዞን ማረሚያ ቤት አስ/ጽ/ቤት ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በማስገባት መወዳደር አለባቸው፡፡
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ከመቶ ሁለት (2%) በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተመስከረለት ቼክ (CPO) እና የምግብ እሕል ናሙና ከጨረታ ሰነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ አለባቸው።
6. በጥቃቅን እና አነስተኛ ንግድ ተደራጅቶ የበሰለ ምግብ ለማቅረብ የሚቀርቡ ማህበራት ቅድሚያ ይሰጣቸዋል። ይህ ካልተገኘ በጥሬ እህል እናወዳድራለን።
7. ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀን በአየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን በስራ ቀን ከረፋዱ በ4፡00 ሰዓት ተጫራቾች ያስገቡበት ሳጥን ታሽጎ በ 4፡30 ሰዓት በዞኑ ማረሚያ ቤት አስ/ፅ/ቤት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው እንዲሁም የህግ ታራሚ ኮሚቴዎች እና የማረሚያ የጨረታ ኮሚቴ አባላት በተገኙበት ይከፈታል፡፡
8. የዞኑ ማረሚያ ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
9. በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በተዘጋጀ ማብሰያ ቤት ውስጥ ምግብ አብስሎ ማቅረብ የሚችል ማረሚያ ቤቱ የሚገኝበት ከተማ
|
ተ.ቁ |
የዞን ማረሚያ ቤት |
የሚገኝበት ከተማ |
|
1 |
የምስራቅ ባሌ ማረሚያ ቤት |
ጊንር |
ለበለጠ መረጃ በስልክ ፣ 0911645276/0911803891 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በኦሮሚያ ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ኮሚሽን የምስራቅ ባሌ ዞን ማረሚያ ቤት አስተዳደር ጽ/ቤት
