በማዕከላዊ ኢት/ያ ክልል በሀዲያ ዞን የጃጁራ ከተማ አስ/ር/ፋ/ጽ/ቤት ለ1ኛ ጃጁራ ቀበሌ ደን አልሚ ማህበረሰብ ደን ማስወገድ ለኤሌክትሪክ ዝርጋታና ትራንስፎርመር ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ለደን ማስወገድ ሽያጭ የወጣ ግልጽ
ጨረታ ማስታወቂያ
በማዕከላዊ ኢት/ያ ክልል በሀዲያ ዞን የጃጁራ ከተማ አስ/ር/ፋ/ጽ/ቤት ለ1ኛ ጃጁራ ቀበሌ ደን አልሚ ማህበረሰብ ደን ማስወገድ ለኤሌክትሪክ ዝርጋታና ትራንስፎርመር ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ አቅራቢዎችን በጨረታ እንዲወዳደሩ ይጋብዛል
ስለዚህ፡-
1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ሥራ ፈቃድ ያለውም ሆነ የሌለውም
ይህ ማስታውቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ተከታታይ በ15 ቀናት ውስጥ የጨረታ ሰነድ 1000 በፊደል /አንድ ሺ ብር/ በጀ/ከ/አስ/ር/ገ/ጽ/ቤት በመክፈል መግዛት የሚቻል ሲሆን ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 300,000 በፊደል /ሶስት መቶ ሺህ ብር/ በጥሬ ገንዘብ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲፒኦ (CPO) የሚጠበቅበቸውን የጨረታ መወዳደሪያ ዋጋ ጽ/ቤቱ ባዘጋጀው ፎርማት ብቻ በመሙላት ሰነድ መግዛት የሚቻል ሲሆን ጨረታው እስከ 15ኛው ቀን 11፡00 ሰዓት የሚያበቃ ሆኖ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ታሽጎ 5፡30 ላይ የሚከፈት ሲሆን የአንዱን ዕቃ ዓይነት ነጠላ ዋጋ በመሙላት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስረጃዎቻችሁን በፖስታ በማሸግ ማስገባት የሚቻል ሆኖ በጀጁራ ከተማ አስ/ር ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 09 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቀኑ በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተባለው ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ይሆናል። ሆኖም ተጫራቹ በራሱ ምርጫ ጨረታው በሚከፈትበት ጊዜ ሳይገኝ መቅረቱ የጨረታውን መከፈት አያስተጓጉልም።
የጨረታ ዝርዝር መረጃ የሚሞላበት ፎርማት ኮፒ ከቢሮ ቁጥር 09 ወይም ከግ/ን/አስ/ር ዋና ሥራ ሂደት እንድትወስዱ እናስታውቃለን፡፡
የደን ባለቤትነት፡- የማህበረሰብ ደን
የደን ዓይነት፡- ቀይ የባህር ዛፍ
የምርት ዓይነት፡- ለግንባታ (ፍልጥ፣ ቋሚና ወራጅ) ለፖልና ለማገዶ
ማሳሰቢያ፡- በደኑ ውስጥ ያሉ ሀገር በቀል ዛፎች ማለትም ዝግባ፣ ዶቅማ እና ሌሎችም መቆረጥ የለባቸውም፡፡
* መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
በማዕከላዊ ኢት/ያ ክልል በሀዲያ ዞን የጃጁራ ከተማ አስ/ር/ፋ/ጽ/ቤት
