በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በደቡብ ወሎ ዞን በወረባቦ ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ተ/ጽ/ቤት በ07 ቀበሌ ገደሮ ልዩ ስሙ ስንጥር እና ባሕር ገንዳ ከሚባል ቦታ የሚገኘውን የባሕርዛፍ እና ጽድ የለማ የማኅበረሰብ ደን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፊልጋል።
የደን ሽያጭ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በደቡብ ወሎ ዞን በወረባቦ ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ተ/ጽ/ቤት በ07 ቀበሌ ገደሮ ልዩ ስሙ ስንጥር እና ባሕር ገንዳ ከሚባል ቦታ የሚገኘውን የባሕርዛፍ እና ጽድ የለማ የማኅበረሰብ ደን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፊልጋል።
1. ለጨረታው የቀረበውን ደን ማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች ለዚሁ ሲባል ለተዘጋጀው የመጫረቻ ሰነድ ላይ በተገለፀው ቦታ ድረስ በመሄድ ጨረታው ለመጀመሪያ ጊዜ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ20 ቀናት ማየት ይችላል።
2. የተዘጋጀውን የመጫረቻ ሰነድ ጨረታውን ባወጣው መ/ቤት በመገኘት ብር 1,000 /አንድ ሺህ ብር/ ብቻ ከፍሎ በሥራ ቀናት ወረባቦ ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ጽ/ቤት መግዛት ይችላል።
3. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የደን አይነት ለመግዛት የሞሉትን ዋጋ 10% የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ በባንክ ክፍያ ማዘዥያ /CPO/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያው ለእያንዳንዱ የደን ዓይነት እና ኮምፓርትመንት ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
4. ተጫራቾች ለመግዛት የሚፈልጉት የእያንዳንዱን የደን ዓይነት እና ኮምፓርትመንት ወይም የሁሉንም ከፍልፋይ የሚገዙበትን ዋጋ ከስማቸውና ከአድራሻቸው ጋር በተናጠል ወይም በአንድ ላይ በፖስታ በማሸግ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በደቡብ ወሎ ዞን የወረባቦ ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ጽ/ቤት የማኅበረሰብ ደን ጨረታ ተብሎ በጉልህ ከተፃፈበት በኋላ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመቁጠር እስከ 20ኛው ቀን ከ4፡00 ሰዓት በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
5. የጨረታው ተወዳዳሪ የፈለገውን ኮምፓርትመንት አንድና ከአንድ በላይ ወይም ሁሉንም ኮምፓርትመንቶች ዋጋ መሙላት ይችላል፡፡
6. የጨረታው ውድድር በኮምፓርትመንቱ በሎት ድምር ስለሆነ የባሕርዛፍና የጽድ ዋጋ መሞላት ሲኖርበት የአንዱ ዋጋ ብቻ መሙላት ከጨረታ ውጭ ያደርጋል።
7. ተጫራቹ ጨረታውን ባሸነፈበት ዋጋ ለገቢዎች ጽ/ቤት 13% የሮያሊቲ ክፍያ የመክፈል ግዴታ አለበት፡፡
8. ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመቁጠር 20ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ ጨረታው ይዘጋል፤ በዚያው ዕለት በ20ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተኙበት 4፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሑድ ወይም በዓላት ቀን ከሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ላይ ይፈፀማል፡፡
9. ለተጨማሪ መረጃ
በስልክ ቁጥር፡- 0901465288/0957887630 ደውለው መጠየቅ ይቻላል።
10. መ/ቤቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በደቡብ ወሎ ዞን የወረባቦ ወረዳ የአካባቢና ደን ጥበቃ ተ/ጽ/ቤት
