የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት ቁርጥራጭ አልሙኒየም እና ቁርጥራጭ ብረቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁርጥራጭ አልሙኒየም እና ቁርጥራጭ ብረቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ከላይ የቀረቡትን ዕቃዎች ጨረታ ባሉበት ሁኔታ መሳተፍ የምትፈልጉ ድርጅቶች ግለሰቦች የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ 11፡00 እና ቅዳሜ እስከ 6፡00 ሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ከፍለ ከተማ ቃሊቲ ማሰልጠኛ ፊት ለፊት የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ቢሮ አጠገብ የኮንስትራከሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት ቢሮ በመቅረብ የተዘጋጀውን የጨረታ ሠነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
1. ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጉትን ቁርጥራጭ አልሙኒየም፤ ቁርጥራጭ ብረቶች የገዙትን የጨረታ ሰነድ በመያዝ በአካል መመልከት ይችላሉ፡፡
2. ተጫራቾች ለመረጡአቸው ዕቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 10 ሺህ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት (City Government OF Addis Ababa Construction Design, Building and Consultation Enterprise) ስም ከታወቀ ባንክ የሚሰጥ ሲፒኦ ወይም የባንክ ዋስትና /un conditional bid bond/ የመወዳደሪያ ሃሳብ ጋር በማያያዝ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
3. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው በትከከል በመሙላት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤ በተጨማሪም ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ሰነድ በታሸገ ኢንቨሎፕ በላዩ ላይ ሙሉ ስምና አድራሻ በመጻፍ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች የሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ዋጋ ተ.እ.ታ /VAT/ የማይጨምር ሲሆን የጨረታ አሸናፊዎች ለሚገዙት ዕቃ ከአሸነፉበት ዋጋ በተጨማሪ የእሴት ታክስ 15% የመክፈል ግዴታ አለባቸው።
5. ጨረታውን ያሸነፉ ተጫራቾች ማሸነፋቸው እንደተገለጸላቸው ያሸነፉበትን ዋጋ በቅድሚያ በመክፈል ጨረታውን ማሸነፋቸውን ከተገለጸበት ቀን አንስቶ በ10 /አስር/ ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ የማንሳት ግዴታ ሲኖርባቸው፤ ይህ ባይሆን ግን ድርጅቱ ጨረታውን ሰርዞ ለማስከበሪያነት የተያዘውን ገንዘብ የሚወርስ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
6. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለአስራ አምስት ተከታታይ የስራ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሆኖ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተዘግቶ በዚሁ እለት ከጠዋቱ 5፡00 በድርጅቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተሳታፊዎች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ላይ ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፡፡
የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቃሊቲ ማሰልጠኛ ፊት ለፊት የኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ቢሮ አጠገብ
ስልክ ቁጥር 0946463816/0912085572
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮንስትራክሽን ዲዛይን፣ ግንባታና ማማከር ድርጅት
