በአፈ/ከሳሽ 1ኛ. አስፋ እና በአፈ/ተከሳሽ 1ኛ. ሐብታሙ ደስታ 2ኛ. አዛለች ደስታ የትዋለ ልክቶ መካከል ባለው የአፈፃፀም ክርክር ጉዳይ በ250 ካ.ሜ ቦታ ላይ ያረፈ ቤት በግልጽ በጨረታ እንዲሸጥ የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት አዟል።
የጨረታ ማስታወቂያ
አፈ/ከሳሽ 1ኛ. አስፋ የትዋለ
አፈ/ተከሳሽ 1ኛ. ሐብታሙ ደስታ
2ኛ. አዛለች ደስታ
መካከል ባለው የአፈፃፀም ክርክር ጉዳይ፤ በዳንግላ ከተማ 02 ቀበሌ አዋሳኙ፣ በምስራቅ- የቦታ ቁጥር 83፤ በምዕራብ መንገድ፣ በሰሜን መንገድ፣ በደቡብ ቦታ ቁጥር 86፤ መካከል በ250 ካ.ሜ ቦታ ላይ ያረፈውና ቤት በፋይል ቁጥር 138/ሀ/296 በቦታ ቁጥር 84 የሚታወቀውን በ1ኛ አፈ/ተከሳሽ ስም የተመዘገበውን ቤት በግልጽ ጨረታ በመነሻ ዋጋ ብር 631,253.38 /ስድስት መቶ ሰላሳ አንድ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ ሶስት ብር ከሰላሳ ስምንት ሳንቲም/ ሆኖ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡30 ባለው ጊዜ ውስጥ በግልጽ በጨረታ እንዲሸጥ የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት ትዕዛዝ በሰጠው መሰረት የዳንግላ ቀበሌ 02 አስተዳደር ጽ/ቤት አንድ ሰው ታዛቢ በመመደብ የዳንግላ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤትም ፀጥታውን የሚያስከብር አንድ ሰው በመመደብ የጨረታው ሥነ-ሥርዓት በአግባቡ እንዲከናወን እንዲደረግ ሆኖ የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሐራጅ ባይም ጨረታውን በበላይነት በመምራት ጨረታው ይካሄዳል፡፡ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ሁሉ ከቦታው ቀርቦ ሕጋዊ መታወቂያ በመያዝ መሳተፍ የሚቻል እና አሸናፊው እንደታወቀ ያሸነፈበትን ከተቻለ ሙሉውን ገንዘብ የሚያስይዝ ካልተቻለም እአንድ አራተኛውን ማስያዝ የሚችል መሆኑን እና ውጤቱንም መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ለሆነው ቀጠሮ እንዲገለጽ።
የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት
