በኢ/ኦ/ተ/ቤ/በአ/አ/ህ/ስ/የደ/ጽጌ/ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በፀበል ቦታ ውስጥ አንድ ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ለመቆፈር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/በአ/አ/ህ/ስ/የደ/ጽጌ/ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን
የጨረታ ቁጥር፡- ደ/ጽ/ቅ/ዑ/220/2018
በኢ/ኦ/ተ/ቤ/በአ/አ/ህ/ስ/የደ/ጽጌ/ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን በፀበል ቦታ ውስጥ አንድ ጥልቅ የውሃ ጉድጓድ ለመቆፈር በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። ስለሆነም ከዚህ በታች የተገለፁትን መስፈርቶች የምታሟሉ እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል።
1. ተጫራቾች በዘርፉ ደረጃ 2 እና ከዛ በላይ የሆነ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ ቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የግብር መለያ ቁጥር ያላቸው።
2. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን (Bid Bond) በደ/ጽጌ/ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ስም ጠቅላላ ዋጋ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
3. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ማለትም ከመጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በደ/ጽጌ/ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ጽ/ቤት በመምጣት ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ትችላላችሁ።
4. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በታሽገ ኢቨሎፕ የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ድረስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
5. ጨረታው ሚያዚያ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወኪሎቻቸው ባሉበት በዕለቱ በ4፡00 ሰዓት በቤተ ክርስቲያኑ ጽ/ቤት ይከፈታል።
6. ደብሩ ጨረታውን በሙሉ/በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- በቦሌ ክፈለ ከተማ፣ ወረዳ 04
የደ/ጽጌ/ቅ/ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን
ለበለጠ መረጃ፡-
ስልክ . 0911383008/0115521974
