በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን በራጴ ወረዳ ፋይናስ እና ፕላን ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዴኦ ዞን በራጴ ወረዳ ፋይናስ እና ፕላን ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህው መሰረት –
1. በዘርፉ ሕጋዊ ፍቃድ ያለው /ያላት
2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያለው/ያላት
3. ፍቃዱን በበጀት ዓመቱ ያሳደሰ /ሰች
4. የቫት ተመዝጋቢ የሆነ/የሆነች
5. የጨረታ ማስከበሪያ 50,000 CPO (ብር ሃምሳ ሺህ) ብር በባንከ የተረጋገጠ ማቅረብ የሚችል፡፡
6. የጨረታ አሸናፊ የሆነ ያሸነፉበትን ዕቃ ወይም የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ራጴ ወረዳ ፋ/ጽ/ቤት ማቅረብ የሚችል።
7. የጨረታው ሰነድ አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ለየብቻ ታሽጎ በአንድ እናት ፖስታ በሰም በማሸግ ማቅረብ የሚችል።
8. ከተራ ቁጥር 1-7 ድረስ የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን ማሟላት የምትችሉ ተጫራቾች ሊያወዳድራችሁ የሚችለውን መረጃ (ሰነድ) በመያዝ ራጴ ወረዳ ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 9 በመቅረብ የማይመለስ 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል የጨረታውን ሰነድ የሚትወሰዱ ሲሆን ጨረታው ለ15 (አስራ አምስት ተከታታይ የስራ ቀናት አየር ላይ ውሎ በ16ኛው ቀን በ4፡00 ታሽጎ በ4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ:- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። የክፈታው ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል፡፡
ለበለጠ መረጃ፡- 09-16-36-46-90
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጌዲኦ ዞን የራጴ ወረዳ ፋይናንስ እና ፕላን ጽ/ቤት
