ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት ከቻይልድፈንድ ኢትዮጵያ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ የሚከተሉትን እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ለሶስተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ተስፋ ብርሃን ህፃናትና ቤተሰብ ልማት ድርጅት ከቻይልድፈንድ ኢትዮጵያ ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ የሚከተሉትን እቃዎች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
መደብ 1: መደብ 1. የአካል ጉዳተኛ ዊልቸር / Stainless steel
Wheel chair made of SS304/
መደብ 2: ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተሮች
በመሆኑም በመስኩ ልምዱ ያላችሁና በሥራው ለመሳተፍ የምትፈልጉ፡-
1) በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ
2) የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት
3) የመልካም ሥራ አፈፃፀም የሚያቀርብ
ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 ተከታታይ ቀናት እና ሰዓት ከድርጅቱ ዋና ጽ/ቤት ቀይት ወይም በኢሜል አድራሻ procurement@tesfab.org በመጠየቅ እያንዳንዱን ሰነድ በማይመለስ ብር 600.00 (ስድስት መቶ) ብቻ የጨረታ ሰነድ በመግዛት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ የጠቅላላ ዋጋውን 1% የባንክ ሲፒኦ ጋር አብሮ በፖስታ በማሸግ እንድትወዳደሩ እየጋበዝን ጨረታው በ7ኛው ቀን ከረፋዱ 4፡30 ሰአት ተዘግቶ በ5፡00 ሰአት ጨረታውን ለመካፈል በተገኙ ተጫራቾች ወይም ወኪሎች ፊት ይከፈታል። 7ኛው ቀን በአል ከሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ሰአት ይከፈታል።
ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በጨረታው አይገደድም።
ለበለጠ መረጃ 251 116 813851 መደወል ይቻላል።
