Tender Detail

Tender Details

  • Company Zemen Insurance S.C (ዘመን ኢንሹራንስ አ.ማ)
  • Address Addis Ababa, Ethiopia, Phone: 251116151493
  • Websitehttps://zemeninsurance.com
  • Deadline02 May 2026, 12:00 AM
  • magazineሪፖርተር
  • Bid Document Price100.00
  • opening date2026-05-02 00:00:00
  • Categories Vehicle , Vehicle Spare Parts

የዘመን ኢንሹራንስ አ/ማ ኩባንያ የካሳ ክፍያ ፈጽሞ የተረከባቸውን ተሽከርካሪዎችና የተሸከርካሪ አካላት እና ሌሎችን ቅሪቶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።


ዘመን ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር

ቁጥር (004/2018)

የጨረታ ማስታወቂያ

 

የዘመን ኢንሹራንስ / ኩባንያ የካሳ ክፍያ ፈጽሞ የተረከባቸውን ተሽከርካሪዎችና የተሸከርካሪ አካላት እና ሌሎችን ቅሪቶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል

ስለሆነም ተሸከርካሪዎቹን የተሸከርካሪ ቅሪት እንዲሁም ሌሎች ቅሪቶችን ለመግዛት የሚፈልጉ ተጫራቾች ቦሌ ኃይሌ እና ዓለም ህንጻ ሁለተኛ ወለል ከሚገኘው ዋና መስሪያ ቤት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነድ በመግዛት አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ሽዋ ዳቦ ወደ ቀኝ ገባ ብሎ በሚገኘው የኩባንያው የተጎዱ ከርካሪዎች ማቆያ (RICOVERY) ውስጥ በማየት ከሚያዚያ 12 ቀን 2018 / እስከ ሚያዚያ 23 ቀን 2018 / ከጠዋቱ 2.00 ሰዓት እስከ 6.00 ሰዓት እንዲሁም ከሰዓት 7.00 ሠዓት እስከ 11.00 ሠዓት ድረስ እንዲሁም ሚያዚያ 24 ቀን 2018 / ከጠዋቱ 4.00 ሰዓት ድረስ ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገቢ ማድረግ ይቻላል

1.     ተጫራቾች ቅሪት ንብረቶችን እና ተሸከርካሪዎቹን ከሚያዝያ 12 ቀን 2018 / አስከ ሚያዚያ 23 ቀን 2018 ድረስ ቃሊቲ በሚገኘው የኩባንያው ሪከቨሪ ጊቢ ውስጥ በመገኘት ማየት ይቻላል

2.     ጨረታው ቅዳሜ ሚያዚያ 24 ቀን 2018 / ከጠዋቱ 4.00 ሰዓት ተዘግቶ በኩባንያው ዋና መስሪያ ቤት ቦሌ ዓለም ህንጻ 2 ፎቅ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሚያዚያ 24 ቀን 2018 / ከጠዋቱ 4.30 ሠዓት ላይ ይከፈታል

3.     ሌሎች ተጫራቾች በሰጡት ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይቻልም

4.     ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ንብረት የመነሻ ዋጋውን 10% (አስር በመቶ) ዘመን ኢንሹራንስ ኩባንያ / ወይም (ZEMEN INSURANCE S.C) ስም በባንክ ክፍያ ማዘዣ (C.P.O) ማስያዝ ይኖርባቸዋል

5.     ከቀረጥ ነጻ ከሆኑት ተሽከርካሪዎች በስተቀር በሌሎች ተሸከርካሪዎች የተሽከርካሪ አካላት ከጨረታው በፊት ዕዳ ቢኖር በኩባንያው ይሸፈናል በጨረታው ለተካተቱት ንብረቶች ከጨረታው በኋላ ያሉትን ማንኛውንም ወጪዎች ገዥው ሙሉ በሙሉ ይሸፍናል

6.     ተጫራቾች የሚያስገቡት ዋጋ ከቫት በፊት መሆን አለበት

7.     የጨረታ አሸናፊዎች ያሸነፉበት ዋጋ ላይ ተጨማሪ ዕሴት ታክስ (VAT) 15% (አስራ አምስት በመቶ) በተጨማሪነት ይከፍላል

8.     አሸናፊዎች የጨረታው ውጤት ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) የሥራ ቀናት ውስጥ ክፍያ ፈጽመው ንብረቶቹን ካልተረከቡ የጨረታው ውጤት የሚስረዝ ሆኖ አላይ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ገንዘብ ለኩባንያው ገቢ ይደረጋል

9.     አሸናፊ ተጫራቾች ተሸከርካሪዎቹንም ሆነ ሌሎች ዕቃዎችን ከሪከቨሪ በራሳቸው ወጪ ሳይነጣጠሉ በአንድ ጊዜ ከፍለው 10 (አስር) ቀናት ውስጥ ንብረቶቹን ከሪከቨሪ መረከብ ይኖርባቸዋል

10. የጨረታው አሸናፊዎች የስም ዝውውር እስከ ስድስት ወር ድረስ ማጠናቀቅ የሚጠበቅባቸው ሲሆን ይህ ሳይሆን ቢቀር ለሚፈጠረው ማንኛውም ጉዳይ (ችግር) ኩባንያው ኃላፊነት አይወስድም

11. ኩባንያው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ በሕግ የተጠበቀ ነው

 

ተጨማሪ ማብራሪያ

ስልክ፡- 09-44-17-36-73 ወይም 09-11-97-95-88 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።

ዘመን ኢንሹራንስ /

አዲስ አበባ

Save Tender