የቤት ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ
የፍርድ ባለመብት ዶ/ር ኃይለልዑል ዘለቀ እና የፍርድ ባለእዳ ወ/ሮ ራሄል አለማየሁ መካከል ስላለው የአፈጻጸም ክርክር አስመልክቶ በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ጐሮ ወረዳ ውስጥ የሚገኝ በ105.528 ካሬ ሜትር በሆነ ላይ ሰፍሮ ያለ የካርታ ቁጥሩ 5079/95 በ18/05/2003 የተሰጠ በፍ ባለዕዳ በወ/ሮ ራሄል አለማየሁ ዋሴ ስም ተመዝግቦ የሚታወቀው በጨረታ ሽያጭ ዋጋ መነሻ ብር 2,624,069.31 (ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሃያ አራት ሺህ ስልሳ ዘጠኝ ብር ከ31/100) በቀን 21/09/2018 ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 6፡00 ሰዓት ግልጽ በሆነ ጨረታ ይሸጣል።
ተጫርቶ መግዛት የሚፈልግ ሰው ካለ የጨረታው መነሻ ለአፈጻጸም ምክንያት የሆነው ቤት ግምት 1/4 CPO ይዞ ጨረታው ይካሄዳል በተባለው ቀንና ሰዓት በዛው ቦታ በመገኘት ተጫርቶ መግዛት የሚችል መሆኑን እናስታውቃለን።
የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቤተሰብ እና ህጻናት ጉዳይ ችሎት
