ኮምፓሸን ኢንተርናሸናል ለድርጅቱ ሥራ የሚያገለግል የአንድ (1) ሃዩንዳይ ኦፍ ሮድ with Off Road Features (የ2025/6 ሞዴል) በጨረታ ግዥ ማድረግ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ኮምፓሸን ኢንተርናሸናል ለድርጅቱ ሥራ የሚያገለግል የአንድ (1) ሃዩንዳይ ኦፍ ሮድ with Off Road Features (የ2025/6 ሞዴል) በጨረታ ግዥ ማድረግ ይፈልጋል።
* ዓይነት (Make): Hyundai
* ሞዴል (Model): ኦፍ ሮድ
* የምርት ዘመን (Model Year): 2026
* ሁኔታ (Condition): ፍጹም አዲስ (o ኪ.ሜ)
* የማሽከርከር ኃይል (Drive Type)፡ 4×4
* ሞተር (Engine)፡ ፔትሮል/ሃይብሪድ (Petrol/Hybrid)
* መሪ (Steering): በግራ በኩል (Left-hand drive) as per Ethiopian law
* ለገጠር እና አስቸጋሪ መንገዶች ተስማሚ የሆነ ከፍታ ያለው።
ስለዚህ በዚህ ጨረታ ስመካፈል ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች
1. ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ የእረፍት ቀኖችን ሳይጨምር ለ3 ተከታታይ የሥራ ቀናት በኮምፓሽን ኢንተርናሽናል ፋይናንስ ክፍል የታደሰ መታወቂያ ፓስፖርት ይዞ በመቅረብ የማይመለስ 500 ብር (አምስት መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሠነድ መግዛት ይኖርባቸዋል።
2. ሰነዱን ለመግዛት የሚመጣ ተጫራች ማንነቱን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ ኦሪጅናል እና ፎቶ ኮፒውን ይዞ መቅረብ ይኖርበታል።
3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከገዙ በኋላ ከጨረታው ቀን በፊት በኮምፓሽን ኢንተርናሽናል ጽ/ቤት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
4. በጨረታው ተሳትፎ ለማድረግ ለጨረታ ማስከበሪያ ዋጋ 10,000.00 በባንክ የተረጋገጠ ማስያዝ አለባቸው።
5. በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ያሸነፈ ከጨረታው ማግስት ጀምሮ በተከታታይ ባሉ 3 የሥራ ቀናት ውል ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል፤
6. የጨረታው አሸናፊ የንብረቱን ጠቅላላ መረጃ ለመስሪያ ቤቱ ለገዢው ያቀርባል፣ የሚያቀርብበት፣ ጊዜ በጨረታው ሰነድ ውል ያሳውቃል።
7. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ4ኛው የሥራ ቀን 4:00 ሰዓት ላይ በኮምፓሽን ኢንተርናሽናል አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ ይከፈታል።
ማሳሰቢያ ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይንም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፦ (ቦሌ ከስካይ ሳይት ሆቴል በስተጀርባ)
ተጨማሪ መረጃ ካስፈለገ በሚቀጥጥው ስልክ ቁጥር ይጠቀሙ
+251 11 554 0447
ኮምፓሽን ኢንተርናሽናል
