የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሥት ግብርና ቢሮ በቢሮው FSHP Progeram ለተለያዩ ዞን እና ወረዳ አገልግሎት የሚውል የሶላር አቅርቦት (ግዥ) እና ተከላ ሥራ አገልግሎት ግዥ አግባብ ካላቸው ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የሶላር ግዥ እና የተከላ ሥራ አገልግሎት ግዥ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 416/18
የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሥት ግብርና ቢሮ በቢሮው FSHP Progeram ለተለያዩ ዞን እና ወረዳ አገልግሎት የሚውል የሶላር አቅርቦት (ግዥ) እና ተከላ ሥራ አገልግሎት ግዥ አግባብ ካላቸው ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የዕቃው/የአገልግሎት ዓይነት |
የመዳረሻና የተከላ ሥራ ቦታ |
ሎት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
የሚታሸግበት ሰዓት |
የሚከፈትበት ሰዓት |
ሰነዱ የሚገኝበት ቦታ |
|
1 |
ሶላር አቅርቦትና ተከላ ሥራ |
ጎፋ ዞን መሎኮዛ ወረዳ |
ሎት-1 |
80,000.00 |
3:00 |
3:30 |
ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ዲላ ከተማ መምህራን ኮሌጅ ግቢ |
|
2 |
ሶላር አቅርቦትና ተከላ ሥራ |
ባኤቶ ዞን ላስካዙሪያ ወረዳ |
ሎት-2 |
40,000.00 |
4:00 |
4:30 |
|
|
3 |
ሶላር አቅርቦትና ተከላ ሥራ |
ጌዲዮ ዞን ገደብ ወረዳ |
ሎት 3 |
300,000.00 |
5:00 |
5:30 |
በመሆኑም በንግድ ሥራ ዘርፉ የታደሰ ፈቃድ፣ የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያለው የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፤ በአቅራቢነት ዝርዝር ዉስጥ ስለመመዝገባቸዉና የቫት ተመዝጋቢነት ማስረጃዎች ያላቸዉና የሚያቀርቡ ተጫራቾች በጨረታዉ መሳተፍ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ለ60 ቀናት የፀና መሆን ይኖርበታል።
በተጫራቾች የሚቀርበዉ የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና መሆን ይኖርበታል። - ተጫራቾች በቢሮዉ የተዘጋጀዉን መደበኛ የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ታትሞ ከወጠበት ቀን ጀምሮ ባለው ተከታታይ 30 ቀናት አስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል በዲላ ከተማ መምህራን ኮሌጅ ግቢ ውስጥ ግብርና ቢሮ የግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ክፍል መውለድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሠነድ በመሙላት የጨረታ የቴክኒካል ኦርጅናልና ና ኮፒ ፋይናንሻል ኦርጅናልና ኮፒ የመጫረቻ ሠነዶችን በአንድ እናት ፖስታ በማዘጋጀት በ31ኛው ቀን ሎት-1 በ3፡00 ሰዓት ሎት-2 በ4፡00 ሎት 3 በ5፡00 በቢሮው ግዥና ንብ/አስ/ ዳይሬክቶሬት ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ። እንዲሁም የጨረታው ሳጥን ለሎት1 በ3:00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ በ3፡30 ለሎት2 4፡00 ታሽጎ በዕለቱ 4፡30 ለሎት3 በ5፡00 ታሽጎ በዕለቱ 5፡30 ተጫራቾች ህጋዊ ተወካዮች በተገኙበት ግዥና ንብ/አስ/ ዳይሬከቶሬት ቢሮ ይከፈታል።
- ቢሮዉ በቀረበዉ ጨረታ ላይ አሸናፊዉ ድርጅት ጋር ዉል ስምምነት ከመፈራረሙ በፊት የግዥዉን 20 ፐርሰንት መቀነስ ወይም መጨመር ይችላል።
- የጨረታው ሳጥን መክፈቻ 31ኛው ቀን የመንግሥት የሥራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በቀጣይ ባለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓትና ቦታ የሚከፈት ይሆናል።
- ቢሮው ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ፡- አንድ ተጫራች መሠዳደር የሚችለው በአንድ ሎት ብቻ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- 046 131 0134/ 09 16 17 65 73 ይጠቀሙ።
የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግሥት ግብርና ቢሮ
